የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ኢንተርፕርነርሽፕ ኢትዮጵያ ያላትን ዕምቅ አቅም ጥቅም ላይ እንድታውል እያደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል

Nov 20, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ ኢንተርፕርነርሽፕ ኢትዮጵያ ያላትን ዕምቅ አቅም ጥቅም ላይ እንድታውል እያደረገ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።

ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል "በጋራ እንገንባ" በሚል መሪ ሀሳብ ከህዳር 8 እስከ 18 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄደውን ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸውም መንግስት የኢንተርፕርነርሽፕ ሥራን ለማስፋት ቁርጠኛ በመሆኑ ዘርፉ ትልቅ ደረጃ ላይ ደርሷል ብለዋል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አመራር የማይበገር ሀገር ለመገንባት ለዘርፉ ትኩረት በመስጠቱ ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል።

ኢንተርፕርነርሽፕ ከሥራ ፈጠራና የሰው ሀይል ልማት ባለፈ ሀገር የመገንባት ጉዳይ መሆኑንም አንስተዋል።

የመደመር መንግሥት ዕሳቤ ተቋማት እሴት መፍጠር እንዳለባቸው ያምናል ያሉት ሚኒስትሯ፤ በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የተመዘገበው ለውጥ ማሳያ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ የኢንተርፕርነርሽፕ ዘርፉን ማገዝ እንደሚገባ በመጠቆም፤ የዘንድሮው የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት እንደሀገር ከያዝነው እሳቤ ጋር ይጣጣማል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ጉዞ ተጀምሯል ያሉት ሚኒስትሯ፣ በእስከ አሁን የተመዘገቡና የታዩ ለውጦች እንደምንችል ማሳያ ናቸው ነው ያሉት።

ጉዟችን የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና እስከሚረጋገጥ በመሆኑ ረጅሙን ጉዞ በፈጠራና ኢንተርፕርነርሽፕ ማገዝ ይገባል ብለዋል።

ዓለም አቀፉ የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት ከህዳር 8 ቀን ጀምሮ ለአስር ተከታታይ ቀናት በተለያዩ ሁነቶች እንደሚካሄድም ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ በኢንተርፕርነርሽፕ ግዙፍ መሆኗን በማንሳት ይህም በዘርፉ በዓለም ሥነ ምህዳር ኢትዮጵያ የሚታይ ስራ እንዳላት ያመለክታል ብለዋል።

መርሀ ግብሩ በዘርፋ ከኢትዮጵያ ጋር አብረው መስራት የሚፈልጉ ተቋማትን የምናገኝበት ይሆናል ያሉ ሲሆን የስታርታፕ አዋጁን ጨምሮ የተወሰዱ እርምጃዎች መንግስት ለዘርፉ እድገት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ያመላክታል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026