የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል የንግዱ ማህበረሰብ እገዛውን ማጎልበት ይጠበቅበታል

Nov 21, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

‎ሀዋሳ፤ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎችን ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል የንግዱ ማህበረሰብ እገዛውን ማጎልበት እንደሚጠበቅበት የከተማው አስተዳደር ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገለጹ።

ሀዋሳን ለኑሮ፣ ለኢንቨስትመንት፣ ለንግድና ለቱሪዝም ተመራጭ ከተማ ለማድረግ ግብ ተይዞ እየተሰራ መሆኑም ተመላክቷል፡፡

ከንቲባው በከተማዋ ከሚገኙ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ጋር በከተማዋ ነባራዊ ሁኔታና ቀጣይ የልማት ትኩረቶች ላይ ዛሬ መክረዋል።


‎በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ በሀዋሳ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የንግዱ ማህበረሰብ ድጋፍና እገዛውን ማጎልበት ይጠበቅበታል፡፡

ከተጀመሩ የለውጥ ሥራዎች አኳያ ከተሞች የሚመሩበት እሳቤ መቀየሩን ያነሱት ከንቲባ ጥራቱ፣ የዜጎችን ህይወት ለሚቀይሩና የኢኮኖሚ እድገትን ማዕከል ላደረጉ ተግባራት ትኩረት እንደሚሰጥ ተናግረዋል፡፡

በሀዋሳ ከተማ የለውጥ ሂደት ውስጥ ፍጥነትና ፈጠራን በማከል ከተማዋን ለንግድና ለኢንቨስትመንት እንዲሁም ለነዋሪዎቿና ለጎብኚዎች ምቹ ለማድረግ ይሰራል ብለዋል።

ለዚህም የሀዋሳ ሐይቅና ሌሎች የተፈጥሮ ሀብቶች፣ የተዘረጉ የመንገድ መሠረተ ልማቶች እንዲሁም እንግዳ ወዳድ ህዝቧ መልካም ዕድሎች መሆናቸውን ነው ከንቲባው ያመላከቱት።

‎በከተማዋ እየተከናወነ ያለው የኮሪደርና ሌሎች የልማት ሥራዎችም ለሀዋሳ የተሻለ አቅም እንደሚፈጥሩ አንስተዋል፡፡

ግብር ከፋዩ ማህበረሰብ የከተማ ዕድገት ሁሉንም ተጠቃሚ እንደሚያደርግ በመረዳት ግብሩን በታማኝነትና በወቅቱ በመክፈል ማሕበራዊ ሃላፊነቱን እንዲወጣና ለልማቱም መፋጠን ተሳትፎውን ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ገልጸዋል፡፡

ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል አቶ አባተ ኪሾ በሰጡት አስተያየት፤ እያደገ የመጣውን የህዝብን የልማት ፍላጎት ለማሟላት ግብራችንን በአግባቡ በመክፈል የሚጠበቅብንን እንወጣለን ብለዋል፡፡


ከአስተዳደሩ ጎን በመቆም የከተማዋን እድገት ለማፋጠን የድርሻቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውን የተናገሩት አቶ ጌቱ ተካ የተባሉ ሌላው የንግዱ ማህበረሰብ አባል ፣ አስተዳደሩ አሰራርን ምቹ ለማድረግ የጀመረውን ስራ እንዲያጠናክር ጠይቀዋል።


በውይይት መድረኩ በከተማዋ የደረጃ “ሀ” ግብር ከፋዮችና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተሳትፈዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026