የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሚያደርግ የዲጂታል እውቀት አግኝተናል-ሰልጣኞች

Nov 24, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

መቀሌ፤ሕዳር 12/2018(ኢዜአ)፡- የኮደርስ ስልጠና መውሰዳችን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሚያደርግ የዲጂታል እውቀት እንድናገኝ አስችሎናል ሲሉ በመቀሌ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ ወጣቶችና ባለሙያዎች ተናገሩ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢንሼቲቩን በይፋ ባስጀመሩበት ወቅት “የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ” መርሐ ግብር በማደግ ላይ ባለው ዲጂታል ኢኮኖሚ ከባቢ የመጪው ትውልድ ኢትዮጵያዊያንን ለማብቃት ታልሞ የተጀመረ መሆኑን መግለፃቸው ይታወሳል።

የኮደርስ ስልጠናው ዓላማም በእውቀት የዳበረ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ትውልድ ማፍራት መሆኑን በማንሳት ወጣቶች የስልጠናው እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማስገንዘባቸው ይታወቃል።

በዚህም መሰረት በሀገሪቷ የተለያዩ አካባቢዎች በተለይም ወጣቶች የኮደርስ ስልጠና በመውሰድ የእድሉ ተጠቃሚ መሆን ችለዋል።


የስልጠናው ተጠቃሚ ከሆኑት መካከልም ወጣት ገነት ጨርቆስ እና ወጣት ሙለይ ኃይሉ ፤ የኮደርስ ስልጠና መውሰዳችን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሚያደርግ የዲጂታል እውቀት እንድናገኝ አስችሎናል ብለዋል።


የኮደርስ ስልጠናውን ከወሰዱት የመንግስት ሰራተኞች መካከል አቶ ሰሎሞን ፀጋይ እና ፍሰሃ ነጋ (ኢንጂነር) የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ለሁላችንም የመጣ ነፃ እድል በመሆኑ በመሰልጠን እውቀት አካብተንበታል ብለዋል።


ከራስ እውቀትም ባለፈ ለተገልጋዩ ህብረተሰብም በቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት ለመስጠት ሥልጠናው እጅግ ጠቃሚ መሆኑንም አንስተዋል።


በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የዲጂታል አቅም ግንባታ ዳይሬክተር አቶ እያሱ ተካ፤ ለወጣቶች የዲጅታል ክህሎት ስልጠና መሰጠቱ ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን ተናግረዋል።


በዚህም መሰረት በትግራይ ክልል እስካሁን ከ30 ሺህ የሚበልጡ ዜጎች የኮደርስ ስልጠና መውሰዳቸውን ጠቁመው በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል።

በቀጣይ ሶስት ዓመታትም ከ200 ሺህ የሚበልጡ ከ12ኛ ክፍል በላይ የሆኑ ተማሪዎችን የስልጠናው ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026