🔇Unmute
መቀሌ፤ሕዳር 12/2018(ኢዜአ)፡- የኮደርስ ስልጠና መውሰዳችን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሚያደርግ የዲጂታል እውቀት እንድናገኝ አስችሎናል ሲሉ በመቀሌ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ ወጣቶችና ባለሙያዎች ተናገሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢንሼቲቩን በይፋ ባስጀመሩበት ወቅት “የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ” መርሐ ግብር በማደግ ላይ ባለው ዲጂታል ኢኮኖሚ ከባቢ የመጪው ትውልድ ኢትዮጵያዊያንን ለማብቃት ታልሞ የተጀመረ መሆኑን መግለፃቸው ይታወሳል።
የኮደርስ ስልጠናው ዓላማም በእውቀት የዳበረ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ትውልድ ማፍራት መሆኑን በማንሳት ወጣቶች የስልጠናው እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማስገንዘባቸው ይታወቃል።
በዚህም መሰረት በሀገሪቷ የተለያዩ አካባቢዎች በተለይም ወጣቶች የኮደርስ ስልጠና በመውሰድ የእድሉ ተጠቃሚ መሆን ችለዋል።

የስልጠናው ተጠቃሚ ከሆኑት መካከልም ወጣት ገነት ጨርቆስ እና ወጣት ሙለይ ኃይሉ ፤ የኮደርስ ስልጠና መውሰዳችን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሚያደርግ የዲጂታል እውቀት እንድናገኝ አስችሎናል ብለዋል።

የኮደርስ ስልጠናውን ከወሰዱት የመንግስት ሰራተኞች መካከል አቶ ሰሎሞን ፀጋይ እና ፍሰሃ ነጋ (ኢንጂነር) የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ለሁላችንም የመጣ ነፃ እድል በመሆኑ በመሰልጠን እውቀት አካብተንበታል ብለዋል።

ከራስ እውቀትም ባለፈ ለተገልጋዩ ህብረተሰብም በቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት ለመስጠት ሥልጠናው እጅግ ጠቃሚ መሆኑንም አንስተዋል።

በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የዲጂታል አቅም ግንባታ ዳይሬክተር አቶ እያሱ ተካ፤ ለወጣቶች የዲጅታል ክህሎት ስልጠና መሰጠቱ ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም መሰረት በትግራይ ክልል እስካሁን ከ30 ሺህ የሚበልጡ ዜጎች የኮደርስ ስልጠና መውሰዳቸውን ጠቁመው በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል።
በቀጣይ ሶስት ዓመታትም ከ200 ሺህ የሚበልጡ ከ12ኛ ክፍል በላይ የሆኑ ተማሪዎችን የስልጠናው ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026