የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ባለስልጣኑ ዲጂታል አሰራሮችን በመዘርጋት ተገልጋዩ ቀልጣፋ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲያገኝ አድርጓል

Nov 24, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ድሬዳዋ፣ህዳር 14/2018(ኢዜአ)፦ዲጂታል አሰራሮችን በመዘርጋት ህብረተሰቡ ፈጣንና ቀልጣፋ የትራስፖርት አገልግሎት እንዲያገኝ እየተጋ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ባለስልጣን ገለፀ።


በባለስልጣኑ የመንገድ ትራፊክ ደህንነትና የመድን ፈንድ ዳይሬክተር ኢንጂነር ሁሴን ጀማል ለኢዜአ እንደገለፁት፥ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የትራንስፖርት ዘርፍ አገልግሎቶችን ፈጣንና ቀልጣፋ ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች እየተመዘገቡ ናቸው።


በተለይም አዲሱ የድሬዳዋ መናኸሪያ ተርሚናል በዘመናዊ መንገድ መገንባቱና ዲጂታል አገልግሎቶች ተደራሽ መደረጋቸው ቀደም ሲል የነበሩ ትርምሶችና መጨናነቆችን አስቀርቷል ብለዋል።


የጉዞ ትኬት በኢ-ቲኬቲንግ አሰራር መቀየሩ፣የትራፊክ ደንብ የሚተላለፉ ቅጣታቸውን በቴሌብር እንዲከፍሉ መደረጉ ከዚህ በፊት ይባክን የነበረን የስራ ጊዜና ጉልበት ማስቀረት አስችሏል ብለዋል።


በተለይም ተጓዦች በተደጋጋሚ ጊዜ ሲያቀርቡ ለነበሩት የተጋነነ የትራንስፖርት ክፍያን በመከላከል ፍትሃዊ እና ተደራሽ አገልግሎቶች እንዲያገኙ ማስቻሉን ገልጸዋል።


እንደ ኢንጂነር ሁሴን ገለፃ፥ ባለስልጣኑ የጀመራቸውን የዲጂታል አገልግሎቶች በማሳደግ ስማርት ድሬዳዋን የሚመጥን አገልግሎቶች ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት ይሰራል።


የባለስልጣኑ የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ዘውገ አውላቸው በበኩላቸው፥ የዲጂታል አገልግሎቶቹ ከድሬዳዋ ወደ ተለያዩ የአገሪቷ አካባቢዎች በሚወጡና በሚገቡ የህዝብ ትራንስፖርቶች እና በከተማዋ ታክሲዎች ላይ ተደራሽ መደረጉን ገልጸዋል።


አሽከርካሪዎች ጉዳያቸውን ካሉበት ስፍራ ሆነው በዲጂታል አገልግሎቱ እየተጠቀሙ ይገኛሉ ብለዋል።


በተጨማሪም የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ትምህርት ቤቶች የትምህርት አሰጣጥን በዲጂታል ካሜራ በመከታተል ብቃትና ስነምግባር የተላበሱ ባለሙያዎችን ለማፍራት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።


ከድሬዳዋ-ሐረር ህዝብ የሚያመላልሰው የሚኒባስ አሽከርካሪ አቶ ሰይፈዲን አልይ እና የታክሲ አሽከርካሪው አቶ ጋሻው ሀብታሙ እንዳሉት፥ ባለስልጣኑ የጀመራቸውን የዲጂታል አገልግሎቶች ጊዜንና ጉልበትን ለስራ በማዋል ውጤታማ ስራ ለመስራት አስችሏቸዋል።


አንድን ጉዳይ ለማስፈፀም ከግማሽ ቀን በላይ ማባከን ቀርቷል ያሉት አስተያየት ሰጪዎቹ፤ ይኸም ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባ ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026