የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

"ልወቅሽ ኢትዮጵያ" ንቅናቄ የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን እያጎለበተ ነው

Nov 28, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ "ልወቅሽ ኢትዮጵያ" የተሰኘው ንቅናቄ የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን በማነቃቃት በኩል ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የቱሪዝም ሚኒስቴር የፕሮሞሽን ዘርፍ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ተሾመ ተክሉ ለኢዜአ እንደገለጹት ልወቅሽ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ትውልዱ ስለ ሀገሩ ባህል፣ ታሪክ እና የቱሪዝም መዳረሻዎች እንዲያውቅ ለማድረግ ያለመ ንቅናቄ ነው።

ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በተለያዩ ከተሞች የ"ልወቅሽ ኢትዮጵያ" የሩጫ ውድድር ባለፉት ዓመታት እየተካሄደ እንደሚገኝ ለአብነት አንስተው ፕሮግራሙ በሀገር ውስጥ ቱሪዝም ላይ ትልቅ ለውጥ እያመጣ መሆኑን ገልጸዋል።

መርሃ ግብሩ ከሩጫው ባሻገር ልዩ የጉብኝት ፓኬጆችን በማዘጋጀት ዜጎች የተፈጥሮና የቅርስ ስፍራዎችን እንዲጎበኙ እያስቻለ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

እንዲሁም በሩጫው ወቅት በሚያልፏባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ታሪካዊና ባህላዊ እሴቶችን እንዲገነዘቡ እያስቻለ መሆኑንም ጨምረው አስታውቀዋል።

ውድድሩ በሚካሄድባቸው ከተሞች፣ የአካባቢው ማኅበረሰብ ከቱሪዝም ፍሰቱ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዲሆን ዕድል እየፈጠረ መሆኑን አንስተዋል፡፡

ከተሞቹ ልዩ ባህሪያቸውንና መስህቦቻቸውን ለብዙኀኑ በማስተዋወቅ የተሻለ ዕውቅና እያገኙ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

ይህ የስፖርትና የቱሪዝም ትስስር የሀገር ውስጥ እንቅስቃሴን ከፍ የሚያደርግ ከመሆኑም በላይ ለሀገራዊ ብልጽግና የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ብለዋል።

የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ኦፕሬሽን ዳይሬክተር ዳግም ተሾመ ፕሮግራሙ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተስፋፋ መምጣቱንና በአሁኑ ጊዜ በስድስት ከተሞች እየተካሄደ እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡

ውድድሩ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች እንዲሁም የውጭ ዜጎች እየተሳተፉበት እንደሚገኙ አንስተው በርካታ ሰዎች በመርሃ ግብሩ ለማሳተፍ ፍላጎታቸውን እያሳዩ እንደሚገኙም አመልክተዋል፡፡

መርሀ ግብሩን በሌሎች የሀገሪቱ ከተሞች ለማስፋት ዕቅድ መያዙንና ኢትዮጵያውያን ሀገራቸውን በደንብ እንዲያውቁ የቱሪዝም ሀብቶችን እንዲጎበኙ ከቱሪዝም ሚኒስቴር ጋር በጋራ እየሰሩ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

የዘንድሮው ልወቅሽ ኢትዮጵያ የሩጫ ውድድር ከጥር ጀምሮ በደብረብርሃን፣ ሀዋሳ፣ ጅማ፣ በቆጂ፣ አርባምንጭ፣ ሀረር ዲስከቨር ኢትዮጵያ ክላሲክ በሚል መሪ ቃል እንደሚካሄድ ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026