የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በክልሉ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን ስኬታማ ለማድረግ የሚያስችል የግብዓት አቅርቦት ተከናውኗል

Nov 28, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ ፤ ሕዳር 19/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን ስኬታማ ለማድረግ የሚያስችል የግብዓት አቅርቦት በወቅቱ መከናወኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ።

የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ በሪሶ ፈይሳ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በዘንድሮው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ከ4 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት ለመሸፈን ርብርብ እየተደረገ ይገኛል።

ይህም በክልሉ በምግብ ራስን ለመቻል ከተቀረጹ ኢንሼቲቮች መካከል መሆኑን ያነሱት ኃላፊው ተግባሩን ለማሳካትም ግብዓት እና ቴክኖሎጂዎች ለአርሶ አደሮች መሰራጨታቸውን ተናግረዋል።


ባለፉት ዓመታት በክልሉ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የውሀ አማራጮችን በመጠቀምና ወቅትን ሳይጠብቁ ለማምረት ለመስኖ ልማት ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል።

ለአብነትም ባለፈው ዓመት ሁለት ሚሊዮን ሄክታር የሚጠጋ መሬትን በበጋ መስኖ ስንዴ በማልማት የተሻለ ምርት መገኘቱን ጠቁመዋል።

ካለፈው ዓመት የተገኘውን ልምድ በመጠቀም በዘንድሮው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ከ4 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ርብርብ መደረጉን ተናግረዋል።

በእስካሁኑ ልማትም አንድ ነጥብ 9 ሚሊዮን ሄክታር መሬት መዘጋጀቱንና የምርት ማሳደጊያ ግብዓትና ምርጥ ዘርም በወቅቱ አርሶ አደሩ ጋር መድረሱን ገልጸዋል።


ለመስኖ ልማቱም ከ3 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ መቅረቡንና ከምርጥ ዘር ድርጅትና ዘር ከሚያባዙ አርሶ አደሮች ጋር ትስስር በመፍጠር የስንዴ ምርጥ ዘር እየቀረበ ይገኛል ብለዋል።

የበጋ መስኖ ስንዴ ልማቱን ለማሳካትም የአፈር ለምነትንና እርጥበትን የሚያሻሽሉ የተፈጥሮ ማዳበሪያን በስፋት አርሶ አደሩ እንዲጠቀም ቀደም ብሎ ግንዛቤ መሰጠቱን አክለዋል።


የዘንድሮውን የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት አብዛኛውን በኩታ ገጠም የእርሻ ስነ ዘዴ ለማልማት መታቀዱንና የዝግጅት ስራውን እስከ ታህሳስ ወር መጨረሻ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል።

ለዚህም ከክልል ጀምሮ በዞንና በወረዳ ያሉ አመራሮች፣ የዘርፉ የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ክትትልና ሙያዊ ድጋፍ እያደረጉ መሆኑንም አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026