🔇Unmute
አዳማ ፤ ሕዳር 19/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን ስኬታማ ለማድረግ የሚያስችል የግብዓት አቅርቦት በወቅቱ መከናወኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ።
የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ በሪሶ ፈይሳ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በዘንድሮው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ከ4 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት ለመሸፈን ርብርብ እየተደረገ ይገኛል።
ይህም በክልሉ በምግብ ራስን ለመቻል ከተቀረጹ ኢንሼቲቮች መካከል መሆኑን ያነሱት ኃላፊው ተግባሩን ለማሳካትም ግብዓት እና ቴክኖሎጂዎች ለአርሶ አደሮች መሰራጨታቸውን ተናግረዋል።

ባለፉት ዓመታት በክልሉ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የውሀ አማራጮችን በመጠቀምና ወቅትን ሳይጠብቁ ለማምረት ለመስኖ ልማት ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል።
ለአብነትም ባለፈው ዓመት ሁለት ሚሊዮን ሄክታር የሚጠጋ መሬትን በበጋ መስኖ ስንዴ በማልማት የተሻለ ምርት መገኘቱን ጠቁመዋል።
ካለፈው ዓመት የተገኘውን ልምድ በመጠቀም በዘንድሮው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ከ4 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ርብርብ መደረጉን ተናግረዋል።
በእስካሁኑ ልማትም አንድ ነጥብ 9 ሚሊዮን ሄክታር መሬት መዘጋጀቱንና የምርት ማሳደጊያ ግብዓትና ምርጥ ዘርም በወቅቱ አርሶ አደሩ ጋር መድረሱን ገልጸዋል።

ለመስኖ ልማቱም ከ3 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ መቅረቡንና ከምርጥ ዘር ድርጅትና ዘር ከሚያባዙ አርሶ አደሮች ጋር ትስስር በመፍጠር የስንዴ ምርጥ ዘር እየቀረበ ይገኛል ብለዋል።
የበጋ መስኖ ስንዴ ልማቱን ለማሳካትም የአፈር ለምነትንና እርጥበትን የሚያሻሽሉ የተፈጥሮ ማዳበሪያን በስፋት አርሶ አደሩ እንዲጠቀም ቀደም ብሎ ግንዛቤ መሰጠቱን አክለዋል።

የዘንድሮውን የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት አብዛኛውን በኩታ ገጠም የእርሻ ስነ ዘዴ ለማልማት መታቀዱንና የዝግጅት ስራውን እስከ ታህሳስ ወር መጨረሻ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል።
ለዚህም ከክልል ጀምሮ በዞንና በወረዳ ያሉ አመራሮች፣ የዘርፉ የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ክትትልና ሙያዊ ድጋፍ እያደረጉ መሆኑንም አስረድተዋል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026