የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በአዲስ አበባ ከተማ የኢንዱስትሪ ምርታማነትን በማሳደግ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን ለመተካት ትኩረት ተሰጥቷል- ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Dec 2, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ህዳር 21/2018(ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ ከተማ የኢንዱስትሪ ምርታማነትን በማሳደግ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን ለመተካት ትኩረት መሰጠቱን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡

የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤና ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር ዓባይ የመዲናዋን የአምራች ኢንዱስትሪ የስራ እንቅስቃሴ ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

በምልከታው ወቅት ከንቲባ አዳነች እንደገለጹት፤ የአምራች ኢንዱስትሪ ምርታማነትን ለማጎልበት ቀጣይነት ያለው የማበረታቻ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ ነው።

በኢንዱስትሪዎች የተፈጠረው ከፍተኛ መነቃቃትም በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ስራ የጀመሩ አምራቾችን ወደ ኢንዱስትሪ ማሸጋገር ያስቻለ ስኬት መመዝገቡን ተናግረዋል።

በዚህም በተኪ የኢንዱስትሪ አቅም በማሳደግ ከሀገር ውስጥ ገበያ ባሻገር ጥራትና ብዛት ያላቸው ምርቶችን ለውጭ ገበያ ማቅረብ ያስቻለ አበረታች ውጤት መመዝገቡን አስረድተዋል።

በአዲስ አበባ በሀገር ውስጥ የኢንዱስትሪ ምርት የተገነቡ የኮሪደር ልማት መሠረተ ልማቶችም የራስን የምርት ውጤት የመጠቀም ባህል እያደገ መምጣቱን አመላካች እንደሆነም አብራርተዋል።

በቀጣይም ከውጭ የሚገቡ የኢንዱስትሪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት አምራቾች በሀገር ሁለንተናዊ የዕድገት ጉዞ ገንቢ ሚናቸውን እንዲወጡ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር ዓባይ፤ በመዲናዋ ከሚገኙ ኢንዱስትሪዎች አብዛኛዎቹ በተኪ ምርት የተሰማሩ ናቸው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ታምርት ሀገር አቀፍ ንቅናቄ በአዲስ አበባ ከተማ በአምራች ኢንዲስትሪ ዘርፍ ለተሰማሩ አምራቾች ከፍተኛ መነቃቃት ጉልህ አስተዋጽኦ መፍጠሩን ገልጸዋል።

በቀጣይም አምራች ኢንዱስትሪዎች የሚያጋጥማቸውን የመስሪያ ቦታ ጥበትና ተያያዥ ጉድለቶች ተገቢውን ምላሽ በመስጠት የምርታማነት አቅምን ለማሳደግ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

በከተማ አስተዳዳሩ የስራ ኃላፈዎችም በብረታ ብረት፣ በጨርቃ ጨርቅ፣ ግንባታ ማሽነሪና ሌሎች አምራቾችን የሥራ እንቅስቃሴ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.