🔇Unmute
አዲስ አበባ ፤ ሕዳር 22/2018 ( ኢዜአ) ፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የግብር ከፋዮችን ቅሬታ ሃላፊዎች በተገኙበት አጣርቶ ምላሽ መስጠት የሚያስችል አሰራር ከመጪው ሐሙስ ጀምሮ ተግባራዊ ያደርጋል፡፡
በአዲስ አበባ የግብር አሰባሰብና የገቢዎች አገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ የሚኖርን ቅሬታ መፍታት የሚያስችል አዲስ አሰራር በከንቲባ ጽ/ቤት ሥር ተዋቅሯል።
አሰራሩ በአስተዳደሩ የገቢዎች ቢሮ ስር በተዘረጋው የቅሬታ አፈታት ሥርዓት ያልረኩ ግብር ከፋዮች ቅሬታዎቻቸውን የሚያቀርቡበት ነው፡፡
በዚህ መሰረትም ከገቢ አሰባሰብ፣ ከሠራተኞች ሥነ ምግባርና አገልግሎት አሰጣጥ ጋር የሚነሱ ቅሬታዎች ዘወትር ሐሙስ ሃላፊዎች በተገኙበት የሚደመጡና ተጣርተው ምላሽ የሚሰጥባቸው ይሆናል፡፡
የተዘረጋው አሰራር ለከንቲባ ጽ/ቤት በሚስጢር ጥቆማ ከሚሰጥበት ነጻ የጥሪ ማዕከል 9977 እና የሚስጢር ሳጥን በተጨማሪ ቅሬታዎችን በአካል ለበላይ አመራር ማቅረብ ያስችላል፡፡
አሰራሩ ከፊታችን ሐሙስ ጀምሮ ወደ ተግባር እንደሚገባ የከተማ አስተዳደሩ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ለኢዜአ የላከው መረጃ ያመለክታል፡፡
ስለሆነም ከመጪው ሐሙስ ሕዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ከገቢዎች ጋር ብቻ የተያያዙ ቅሬታዎችን አመራሩ ተቀብሎ እንደሚያስተናግድ ተጠቁሟል፡፡
Jul 17, 2025
Apr 24, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፦ የሲሚንቶ ንግድ እና መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎችን በተመለከተ የወጡ መመሪያዎች ገበያውን በማረጋጋትና የዋጋ ግሽበትን በመቀ...
Feb 12, 2025