የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በጨፋ ሮቢት ከተማ ከ33 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተለያዩ መሰረተ ልማቶች ግንባታ እየተካሄደ ነው

Dec 3, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ጨፋ ሮቢት፤ ህዳር 23/2018(ኢዜአ )፡- በጨፋ ሮቢት ከተማ ከ33 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተለያዩ መሰረተ ልማቶች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን የከተማው ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሰይድ መሀመድ ገለፁ።

የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ፣ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ሌሎችም ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በአማራ ክልል በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ጨፋ ሮቢት ከተማ አስተዳደር የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።


የከተማው ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሰይድ መሀመድ በወቅቱ እንደገለፁት በከተማው ህብረተሰቡን በማስተባበር የተለያዩ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ነው።

በዘንድሮው በጀት ዓመት ከ33 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የጌጠኛ ድንጋይ ንጣፍ ጨምሮ የመንገድ፣ የፍሳሽ መውረጃና የሌሎች የመሰረተ ልማቶች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል ።

በተጨማሪም የአቅመ ደካማ ህብረተሰብ ክፍሎች መኖሪያ ቤቶች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን አመልክተዋል ።

የመሰረት ልማቶች በተያዘላቸው ጊዜ በጥራት ተገንብተው እንዲጠናቀቁ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል።


ሚኒስትሮቹን ጨምሮ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎቹ የጨፋ ሮቢት የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን የስራ እንቅስቃሴም ተመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.