🔇Unmute
ጨፋ ሮቢት፤ ህዳር 23/2018(ኢዜአ )፡- በጨፋ ሮቢት ከተማ ከ33 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተለያዩ መሰረተ ልማቶች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን የከተማው ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሰይድ መሀመድ ገለፁ።
የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ፣ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ሌሎችም ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በአማራ ክልል በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ጨፋ ሮቢት ከተማ አስተዳደር የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።

የከተማው ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሰይድ መሀመድ በወቅቱ እንደገለፁት በከተማው ህብረተሰቡን በማስተባበር የተለያዩ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ነው።
በዘንድሮው በጀት ዓመት ከ33 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የጌጠኛ ድንጋይ ንጣፍ ጨምሮ የመንገድ፣ የፍሳሽ መውረጃና የሌሎች የመሰረተ ልማቶች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል ።
በተጨማሪም የአቅመ ደካማ ህብረተሰብ ክፍሎች መኖሪያ ቤቶች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን አመልክተዋል ።
የመሰረት ልማቶች በተያዘላቸው ጊዜ በጥራት ተገንብተው እንዲጠናቀቁ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል።

ሚኒስትሮቹን ጨምሮ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎቹ የጨፋ ሮቢት የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን የስራ እንቅስቃሴም ተመልክተዋል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026