የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በጨፋ ሮቢት ከተማ ከ33 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተለያዩ መሰረተ ልማቶች ግንባታ እየተካሄደ ነው

Dec 3, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ጨፋ ሮቢት፤ ህዳር 23/2018(ኢዜአ )፡- በጨፋ ሮቢት ከተማ ከ33 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተለያዩ መሰረተ ልማቶች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን የከተማው ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሰይድ መሀመድ ገለፁ።

የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ፣ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ሌሎችም ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በአማራ ክልል በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ጨፋ ሮቢት ከተማ አስተዳደር የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።


የከተማው ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሰይድ መሀመድ በወቅቱ እንደገለፁት በከተማው ህብረተሰቡን በማስተባበር የተለያዩ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ነው።

በዘንድሮው በጀት ዓመት ከ33 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የጌጠኛ ድንጋይ ንጣፍ ጨምሮ የመንገድ፣ የፍሳሽ መውረጃና የሌሎች የመሰረተ ልማቶች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል ።

በተጨማሪም የአቅመ ደካማ ህብረተሰብ ክፍሎች መኖሪያ ቤቶች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን አመልክተዋል ።

የመሰረት ልማቶች በተያዘላቸው ጊዜ በጥራት ተገንብተው እንዲጠናቀቁ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል።


ሚኒስትሮቹን ጨምሮ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎቹ የጨፋ ሮቢት የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን የስራ እንቅስቃሴም ተመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026