🔇Unmute
ድሬደዋ፣ ህዳር 23/2018(ኢዜአ)፡- ድሬደዋን ውብና ተመራጭ የመኖሪያ እና የስራ ማዕከል ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የከተማው ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ጀማል ኢብራሂም ተናገሩ።
ኢንጂነር ጀማል ይህን የተናገሩት በከተማዋ እየተካሄዱ በሚገኙ የኮሪደር እና ሌሎች ልማቶች ላይ የህብረተሰቡን ተሳትፎ ለማሳደግ ያለመ ውይይት ላይ ነው።

ኢንጂነር ጀማል በወቅቱ እንደተናገሩት፤ ድሬደዋ ውብና ተመራጭ የስራና የመኖሪያ ማዕከል ለማድረግ እየተከናወኑ የሚገኙ ልማቶች ተጨባጭ ውጤቶች አምጥተዋል።
በተለይም በመጀመሪያ ምዕራፍ በህዝብ ተሳትፎ እየተጠናቀቀ የሚገኘው 11 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ከተማዋን ውብ የስራና ለመኖሪያ ተመራጭ እያደረጋት ይገኛል ብለዋል።
በተጨማሪም በዲጂታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ የህዝብን አገልግሎቶች ፈጣንና ቀልጣፋ በማድረግ ስማርት ከተማን የመፍጠሩ ሂደት በስኬት እየተጓዘ መሆኑን በመግለፅ።
እነዚህን ውጤቶች በፈጠራና በፍጥነት በላቀ ደረጃ ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው የማጠናቀቂያ ስራ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር እና ሌሎች ፕሮጀክቶች ዳር እንዲደርሱ ነዋሪው የድርሻቸውን ሚና እንዲያጠናክር ጠይቀዋል።

በውይይቱ ላይ የተሳተፉት የንግዱ ማህበረሰብና ነዋሪዎች በበኩላቸው በከተማዋ እየተሰሩ የሚገኙ የኮሪደር ልማቶች የድሬዳዋን ገፅታና ውበት ያረጋገጡ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ከተሳታፊዎቹ መካከል ወይዘሮ እታፈራው አለማየሁ እና መሐመድ ኢድሪስ እንዳሉት ልማቱ የሚፈለገውን ውጤት እንዲያስገኝ አካባቢያቸውን በማስዋብ የድርሻቸውን ኃላፊነት እየተወጡ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
የሚሰሩት የከተማ ልማቶች ወጪ ቆጣቢና ከብክነት የፀዱ እንዲሆኑ የመሠረተ ልማት አቅራቢ ተቋማት የተቀናጀ እና የተናበበ ስራ መስራት እንዳለባቸውም ጠይቀዋል።
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...
Apr 14, 2026
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026