🔇Unmute
ድሬደዋ፣ ህዳር 23/2018(ኢዜአ)፡- ድሬደዋን ውብና ተመራጭ የመኖሪያ እና የስራ ማዕከል ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የከተማው ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ጀማል ኢብራሂም ተናገሩ።
ኢንጂነር ጀማል ይህን የተናገሩት በከተማዋ እየተካሄዱ በሚገኙ የኮሪደር እና ሌሎች ልማቶች ላይ የህብረተሰቡን ተሳትፎ ለማሳደግ ያለመ ውይይት ላይ ነው።

ኢንጂነር ጀማል በወቅቱ እንደተናገሩት፤ ድሬደዋ ውብና ተመራጭ የስራና የመኖሪያ ማዕከል ለማድረግ እየተከናወኑ የሚገኙ ልማቶች ተጨባጭ ውጤቶች አምጥተዋል።
በተለይም በመጀመሪያ ምዕራፍ በህዝብ ተሳትፎ እየተጠናቀቀ የሚገኘው 11 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ከተማዋን ውብ የስራና ለመኖሪያ ተመራጭ እያደረጋት ይገኛል ብለዋል።
በተጨማሪም በዲጂታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ የህዝብን አገልግሎቶች ፈጣንና ቀልጣፋ በማድረግ ስማርት ከተማን የመፍጠሩ ሂደት በስኬት እየተጓዘ መሆኑን በመግለፅ።
እነዚህን ውጤቶች በፈጠራና በፍጥነት በላቀ ደረጃ ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው የማጠናቀቂያ ስራ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር እና ሌሎች ፕሮጀክቶች ዳር እንዲደርሱ ነዋሪው የድርሻቸውን ሚና እንዲያጠናክር ጠይቀዋል።

በውይይቱ ላይ የተሳተፉት የንግዱ ማህበረሰብና ነዋሪዎች በበኩላቸው በከተማዋ እየተሰሩ የሚገኙ የኮሪደር ልማቶች የድሬዳዋን ገፅታና ውበት ያረጋገጡ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ከተሳታፊዎቹ መካከል ወይዘሮ እታፈራው አለማየሁ እና መሐመድ ኢድሪስ እንዳሉት ልማቱ የሚፈለገውን ውጤት እንዲያስገኝ አካባቢያቸውን በማስዋብ የድርሻቸውን ኃላፊነት እየተወጡ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
የሚሰሩት የከተማ ልማቶች ወጪ ቆጣቢና ከብክነት የፀዱ እንዲሆኑ የመሠረተ ልማት አቅራቢ ተቋማት የተቀናጀ እና የተናበበ ስራ መስራት እንዳለባቸውም ጠይቀዋል።
Jul 17, 2025
Apr 24, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፦ የሲሚንቶ ንግድ እና መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎችን በተመለከተ የወጡ መመሪያዎች ገበያውን በማረጋጋትና የዋጋ ግሽበትን በመቀ...
Feb 12, 2025