🔇Unmute
ድሬደዋ፣ ህዳር 23/2018(ኢዜአ)፡- ድሬደዋን ውብና ተመራጭ የመኖሪያ እና የስራ ማዕከል ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የከተማው ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ጀማል ኢብራሂም ተናገሩ።
ኢንጂነር ጀማል ይህን የተናገሩት በከተማዋ እየተካሄዱ በሚገኙ የኮሪደር እና ሌሎች ልማቶች ላይ የህብረተሰቡን ተሳትፎ ለማሳደግ ያለመ ውይይት ላይ ነው።

ኢንጂነር ጀማል በወቅቱ እንደተናገሩት፤ ድሬደዋ ውብና ተመራጭ የስራና የመኖሪያ ማዕከል ለማድረግ እየተከናወኑ የሚገኙ ልማቶች ተጨባጭ ውጤቶች አምጥተዋል።
በተለይም በመጀመሪያ ምዕራፍ በህዝብ ተሳትፎ እየተጠናቀቀ የሚገኘው 11 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ከተማዋን ውብ የስራና ለመኖሪያ ተመራጭ እያደረጋት ይገኛል ብለዋል።
በተጨማሪም በዲጂታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ የህዝብን አገልግሎቶች ፈጣንና ቀልጣፋ በማድረግ ስማርት ከተማን የመፍጠሩ ሂደት በስኬት እየተጓዘ መሆኑን በመግለፅ።
እነዚህን ውጤቶች በፈጠራና በፍጥነት በላቀ ደረጃ ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው የማጠናቀቂያ ስራ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር እና ሌሎች ፕሮጀክቶች ዳር እንዲደርሱ ነዋሪው የድርሻቸውን ሚና እንዲያጠናክር ጠይቀዋል።

በውይይቱ ላይ የተሳተፉት የንግዱ ማህበረሰብና ነዋሪዎች በበኩላቸው በከተማዋ እየተሰሩ የሚገኙ የኮሪደር ልማቶች የድሬዳዋን ገፅታና ውበት ያረጋገጡ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ከተሳታፊዎቹ መካከል ወይዘሮ እታፈራው አለማየሁ እና መሐመድ ኢድሪስ እንዳሉት ልማቱ የሚፈለገውን ውጤት እንዲያስገኝ አካባቢያቸውን በማስዋብ የድርሻቸውን ኃላፊነት እየተወጡ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
የሚሰሩት የከተማ ልማቶች ወጪ ቆጣቢና ከብክነት የፀዱ እንዲሆኑ የመሠረተ ልማት አቅራቢ ተቋማት የተቀናጀ እና የተናበበ ስራ መስራት እንዳለባቸውም ጠይቀዋል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026