የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ኢትዮጵያ ስሟንና ታሪኳን የሚመጥኑ በርካታ ትልልቅ ፕሮጀክቶችን ጀምራ መጨረስ የምትችል ሀገር ሆናለች

Dec 8, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ህዳር 27/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ስሟንና ታሪኳን የሚመጥኑ በርካታ ትልልቅ ፕሮጀክቶችን ጀምራ መጨረስ የምትችል ሀገር መሆኗን በአዲስ አበባ ከተማ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ በተካሄደው ህዝባዊ መድረክ የተሳተፉ የህብረተሰብ ክፍሎች ገለጹ።

በዛሬው እለት በአዲስ አበባ የተለያዩ ክፍለ ከተሞች የተካሄደው ህዝባዊ ውይይት በቂርቆስ ክፍለ-ከተማም ተከናውኗል።

በውይይት መድረኩ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።


"የጉባ ብስራቶች፣ የመደመር መንግስት ትሩፋቶች" በሚል መሪ ሀሳብ በተካሄደው ህዝባዊ ውይይቱ ላይ ነዋሪዎቹ በኢትዮጵያ በርካታ የልማት ውጤቶች ተመዝግበዋል ሲሉ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ስሟንና ታሪኳን የሚመጥኑ በርካታ ትልልቅ ፕሮጀክቶችን ጀምራ መጨረስ የምትችል ሀገር ሆናለች ያሉት ተወያዮቹ ለዚህም በመንግስት በኩል የተሰጠው ትኩረትና የአመራር ቁርጠኝነት ውጤት ስለሆነ ሊመሰገን ይገባዋል ብለዋል።

እንደሀገር የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ሊደገፉ የሚገባቸው መሆኑን ጠቁመው፤ የመኖሪያ ቤት ግንባታን ማጠናከር፣ የሥራ ዕድል ፈጠራን ማስፋፋት እና የኑሮ ውድነትን ማረጋጋት ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውም ጠቁመዋል፡፡

ውይይቱን የመሩት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) በውይይቱ የተነሱ ጉዳዮች ላይ መንግስት በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል።

መንግስት አስቀድሞ በሁሉም አካባቢዎች የጀመራቸውና የህዝቡን ኑሮ የሚያሻሽሉ ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።

አመራሮቹ የመደመር መንግሥት ግብ በሀገራቸው የሚኮሩ ቅን ኢትዮጵያውያንን መፍጠር መሆኑን ገልጸው፤ የዜጎችን ቀጥተኛ ተጠቃሚነትና የኑሮ ደረጃ ማሻሻል ላይ ያተኮሩ ሰው ተኮር ፕሮጀክቶች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል፡፡

ህብረ ብሔራዊት ኢትዮጵያ በመደመር ወደ ሁለንተናዊ ብልፅግና የምታደርገው ጉዞ አጠናክራ መቀጠል አለባት ሲሉም ተሳታፊዎቹ ገልፀዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026