የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የአዲስ አበባ የልማት ስኬቶች የነዋሪዎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ የከተማዋን ዕድገትና ገጽታ የገለጡ ናቸው

Dec 8, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ህዳር 27/2018(ኢዜአ)፦ የመዲናዋ የልማት ስኬቶች የነዋሪዎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ የከተማዋን ዕድገትና ገጽታ የገለጡ መሆናቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ3ኛ ዙር ሰልጣኝ አመራሮች ገለጹ፡፡

''በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እመርታ'' ሶስተኛ ዙር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰልጣኝ አመራሮች በመዲናዋ የተከናወኑና በግንባታ ላይ የሚገኙ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል።

አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ የጉብኝቱ ተሳታፊዎች መካከል በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ አምስት የኢንስፔክስንና ሥነ-ምግባር ኮሚሽን ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሃይለየሱስ ባልከው፤ በአዲስ አበባ የተገኙ የልማት ስኬቶች መንግስት ለህዝብ የገባውን ቃል ምላሽ የሰጠበት ነው ብለዋል።

በዚህም የአዲስ አበባ የልማት ስኬቶች አዳዲስ የመዝናኛ፣ የመንገድ፣ የትራፊክ ማሳለጫና ሌሎች የመሰረተ ልማት ተግባራት መዲናዋን በሁሉም ዘርፍ በማዘመን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እያደረጋት መሆኑን ገልጸዋል።

በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት አፈ-ጉበዔ ብዟየሁ ገሰሰ በበኩላቸው፤ የመደመር መንግስት እሳቤ የአዲስ አበባን ዕድገትና ገጽታ በተግባር መግለጡን ተናግረዋል።

በቀጣይም የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስድስት የፋይናንስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ላግ ቲኮ በበኩላቸው፤ የቆሻሻ መጣያ የነበሩ ስፍራዎች አሁን ላይ የመዝናኛና የቱሪስት መዳረሻ ለመሆን በቅተዋል ብለዋል።

በአዲስ አበባ የተገነቡ በሂደት ላይ የሚገኙ የልማት ሥራዎች የነዋሪዎችን የሥራ ዕድል ፈጠራና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጡ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቤዛዊት ጌታቸው፤ በወንዝ ዳር፣ በመንገድ፣ በመዝናኛ ስፍራና በመኖሪያ ቤት ግንባታ ላይ የተሰሩ ስራዎች አስደናቂ ናቸው ብለዋል፡፡

በመዲናዋ የተሰሩ ስራዎች ሁሉ ሰው ተኮር መሆናቸውን ተመልክቻለው ያሉት ደግሞ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት የሚዲያ ዘርፍ ኃላፊ ብሩክ መንግስቱ ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የማዕድን ሀብት ልማት ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ አቅም እየሆነ ነው

ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...

Jun 10, 2026

የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ የሕዝብን ሀብት ለልማት በማዋል በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...

Jun 9, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...

May 28, 2026

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026