የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የአዲስ አበባ የልማት ስኬቶች የነዋሪዎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ የከተማዋን ዕድገትና ገጽታ የገለጡ ናቸው

Dec 8, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ህዳር 27/2018(ኢዜአ)፦ የመዲናዋ የልማት ስኬቶች የነዋሪዎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ የከተማዋን ዕድገትና ገጽታ የገለጡ መሆናቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ3ኛ ዙር ሰልጣኝ አመራሮች ገለጹ፡፡

''በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እመርታ'' ሶስተኛ ዙር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰልጣኝ አመራሮች በመዲናዋ የተከናወኑና በግንባታ ላይ የሚገኙ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል።

አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ የጉብኝቱ ተሳታፊዎች መካከል በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ አምስት የኢንስፔክስንና ሥነ-ምግባር ኮሚሽን ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሃይለየሱስ ባልከው፤ በአዲስ አበባ የተገኙ የልማት ስኬቶች መንግስት ለህዝብ የገባውን ቃል ምላሽ የሰጠበት ነው ብለዋል።

በዚህም የአዲስ አበባ የልማት ስኬቶች አዳዲስ የመዝናኛ፣ የመንገድ፣ የትራፊክ ማሳለጫና ሌሎች የመሰረተ ልማት ተግባራት መዲናዋን በሁሉም ዘርፍ በማዘመን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እያደረጋት መሆኑን ገልጸዋል።

በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት አፈ-ጉበዔ ብዟየሁ ገሰሰ በበኩላቸው፤ የመደመር መንግስት እሳቤ የአዲስ አበባን ዕድገትና ገጽታ በተግባር መግለጡን ተናግረዋል።

በቀጣይም የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስድስት የፋይናንስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ላግ ቲኮ በበኩላቸው፤ የቆሻሻ መጣያ የነበሩ ስፍራዎች አሁን ላይ የመዝናኛና የቱሪስት መዳረሻ ለመሆን በቅተዋል ብለዋል።

በአዲስ አበባ የተገነቡ በሂደት ላይ የሚገኙ የልማት ሥራዎች የነዋሪዎችን የሥራ ዕድል ፈጠራና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጡ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቤዛዊት ጌታቸው፤ በወንዝ ዳር፣ በመንገድ፣ በመዝናኛ ስፍራና በመኖሪያ ቤት ግንባታ ላይ የተሰሩ ስራዎች አስደናቂ ናቸው ብለዋል፡፡

በመዲናዋ የተሰሩ ስራዎች ሁሉ ሰው ተኮር መሆናቸውን ተመልክቻለው ያሉት ደግሞ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት የሚዲያ ዘርፍ ኃላፊ ብሩክ መንግስቱ ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026