🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 28/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ለግብርናው ዘርፍ በሰጠችው ልዩ ትኩረት በከፍተኛ ደረጃ የምርታማነት ስኬት በማስመዝገብ ላይ ትገኛለች ሲል መቀመጫውን ሳውዲ አረቢያ ያደረገው አሻርቅ ኒውስ ዘግቧል።
ኢትዮጵያ ከውጭ ሀገራት የስንዴ ዕርዳታ መቀበል ማቆሟን በይፋ ካወጀች በኋላ በስንዴ ምርት ሙሉ ለሙሉ ራሷን መቻሏል አትቷል።

ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቁጥር አንድ የስንዴ አምራች በመሆን ታሪክ ሰርታለች ያለው ሚዲያው፥ መንግሥት የተከተለው የግብርና ፖሊሲ የስንዴ ምርትን በዕጥፍ ለማሳደጉ አንዱ ምክንያት መሆኑን አንስቷል።
በተጨማሪም፥ ኢትዮጵያ በስንዴ ምርታማነት ላስመዘገበችው ትልቅ ስኬት ሶስት ምክንያቶችን አስፍሯል፥ እነሱም፦ከፍተኛ የመስኖ እርሻ መስፋፋት፣የተሻሻሉ ምርጥ ዘሮችንና ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀሙእንዲሁም መንግሥት የምግብ ምርትን የሚደግፍ ፖሊሲ መተግበሩ ይህን አስገራሚ ለውጥ እንዲያመጣ አስችሎታል ብሏል።

ኢትዮጵያ ካላት 112 ሚሊየን ሔክታር መሬት ውስጥ 38 ሚሊዮን ሔክታር የሚጠጋው ለግብርና ምቹ መሆኑንም ገልጿል።
ሀገሪቱ በአንድ የግብርና ወቅት ብቻ 100 ሚሊዮን ቶን የሚደርስ ስንዴ የማምረት አቅም እንዳላት ነው አሻርቅ በትንታኔው የገለጸው።

የሀገሪቱ ዓመታዊ የስንዴ ፍጆታ ከ8 ሚሊየን ቶን የሚበልጥ ባለመሆኑ የሚተርፈውን ስንዴ ወደ ውጭ ሀገራት በመላክ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት እንደምትችል አክሏል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026