የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ኢትዮጵያ ለግብርናው ዘርፍ በሰጠችው ልዩ ትኩረት በከፍተኛ ደረጃ ስኬት በማስመዝገብ ላይ ትገኛለች

Dec 8, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 28/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ለግብርናው ዘርፍ በሰጠችው ልዩ ትኩረት በከፍተኛ ደረጃ የምርታማነት ስኬት በማስመዝገብ ላይ ትገኛለች ሲል መቀመጫውን ሳውዲ አረቢያ ያደረገው አሻርቅ ኒውስ ዘግቧል።

ኢትዮጵያ ከውጭ ሀገራት የስንዴ ዕርዳታ መቀበል ማቆሟን በይፋ ካወጀች በኋላ በስንዴ ምርት ሙሉ ለሙሉ ራሷን መቻሏል አትቷል።


ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቁጥር አንድ የስንዴ አምራች በመሆን ታሪክ ሰርታለች ያለው ሚዲያው፥ መንግሥት የተከተለው የግብርና ፖሊሲ የስንዴ ምርትን በዕጥፍ ለማሳደጉ አንዱ ምክንያት መሆኑን አንስቷል።

በተጨማሪም፥ ኢትዮጵያ በስንዴ ምርታማነት ላስመዘገበችው ትልቅ ስኬት ሶስት ምክንያቶችን አስፍሯል፥ እነሱም፦ከፍተኛ የመስኖ እርሻ መስፋፋት፣የተሻሻሉ ምርጥ ዘሮችንና ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀሙእንዲሁም መንግሥት የምግብ ምርትን የሚደግፍ ፖሊሲ መተግበሩ ይህን አስገራሚ ለውጥ እንዲያመጣ አስችሎታል ብሏል።


ኢትዮጵያ ካላት 112 ሚሊየን ሔክታር መሬት ውስጥ 38 ሚሊዮን ሔክታር የሚጠጋው ለግብርና ምቹ መሆኑንም ገልጿል።

ሀገሪቱ በአንድ የግብርና ወቅት ብቻ 100 ሚሊዮን ቶን የሚደርስ ስንዴ የማምረት አቅም እንዳላት ነው አሻርቅ በትንታኔው የገለጸው።


የሀገሪቱ ዓመታዊ የስንዴ ፍጆታ ከ8 ሚሊየን ቶን የሚበልጥ ባለመሆኑ የሚተርፈውን ስንዴ ወደ ውጭ ሀገራት በመላክ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት እንደምትችል አክሏል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026