🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 28/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ለግብርናው ዘርፍ በሰጠችው ልዩ ትኩረት በከፍተኛ ደረጃ የምርታማነት ስኬት በማስመዝገብ ላይ ትገኛለች ሲል መቀመጫውን ሳውዲ አረቢያ ያደረገው አሻርቅ ኒውስ ዘግቧል።
ኢትዮጵያ ከውጭ ሀገራት የስንዴ ዕርዳታ መቀበል ማቆሟን በይፋ ካወጀች በኋላ በስንዴ ምርት ሙሉ ለሙሉ ራሷን መቻሏል አትቷል።

ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቁጥር አንድ የስንዴ አምራች በመሆን ታሪክ ሰርታለች ያለው ሚዲያው፥ መንግሥት የተከተለው የግብርና ፖሊሲ የስንዴ ምርትን በዕጥፍ ለማሳደጉ አንዱ ምክንያት መሆኑን አንስቷል።
በተጨማሪም፥ ኢትዮጵያ በስንዴ ምርታማነት ላስመዘገበችው ትልቅ ስኬት ሶስት ምክንያቶችን አስፍሯል፥ እነሱም፦ከፍተኛ የመስኖ እርሻ መስፋፋት፣የተሻሻሉ ምርጥ ዘሮችንና ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀሙእንዲሁም መንግሥት የምግብ ምርትን የሚደግፍ ፖሊሲ መተግበሩ ይህን አስገራሚ ለውጥ እንዲያመጣ አስችሎታል ብሏል።

ኢትዮጵያ ካላት 112 ሚሊየን ሔክታር መሬት ውስጥ 38 ሚሊዮን ሔክታር የሚጠጋው ለግብርና ምቹ መሆኑንም ገልጿል።
ሀገሪቱ በአንድ የግብርና ወቅት ብቻ 100 ሚሊዮን ቶን የሚደርስ ስንዴ የማምረት አቅም እንዳላት ነው አሻርቅ በትንታኔው የገለጸው።

የሀገሪቱ ዓመታዊ የስንዴ ፍጆታ ከ8 ሚሊየን ቶን የሚበልጥ ባለመሆኑ የሚተርፈውን ስንዴ ወደ ውጭ ሀገራት በመላክ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት እንደምትችል አክሏል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026