የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በመንግስት እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ተግባራት የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጡ ነው

Dec 8, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

‎ባሕርዳር ፤ ሕዳር 28/2018 (ኢዜአ) ፡- በመደመር መንግስት እይታ በተለያዩ ዘርፎች እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ተግባራት ሀገራዊ ዕድገቱን ከማፋጠን ባለፈ የሕብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጡ መሆናቸውን በአማራ ክልል የሰሜን ጎጃም ዞን እና የባሕር ዳር ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።

መንግስት የሀገሪቱን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ይበይናሉ ተብሎ ትኩረት ከሰጣቸው ዋና ዋና የልማት ዘርፎች ግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ የከተማና መሰረተ ልማት፣ ማዕድንና ቱሪዝም ይጠቀሳሉ።

የሰሜን ጎጃም ዞን የጎንጂቆለላ ወረዳ ነዋሪዎች ውስጥ አቶ አዳነ አለምኔ፤ የመደመር መንግስት በግብርናው ዘርፍ ሰፋፊና ውጤታማ የልማት ተግባራት እንዲከናወኑ እያስቻለ ይገኛል ብለዋል።


‎‎በተለይ በገጠር ኮሪደር ልማት በግብርናው ዘርፍ በሰብል ልማት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ፣ በእንስሳት እርባታ፣ በተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ፣ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ትኩረት ተደርጎ በመስራቱ አበረታች ኢኮኖሚያዊ ዕድገት እንዲመጣ እያገዘ መሆኑን ገልጸዋል።

‎‎ሜካናይዜሽንን በማስፋፋት ኋላቀር የሆነውን የግብርና አሰራር በመቀየር በግብርናው ዘርፍ መዋቅራዊ ለውጥ እንዲመጣ ማስቻሉም አንስተዋል።

‎‎በከተማ ልማት ዘርፍ ደግሞ ከተሞችን ፅዱና ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እየተደረገ ያለው ጥረት ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ እያደረገ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል።

‎‎በቀጣይም ሰላምን አፅንቶ ከማዝለቅ ጎን ለጎን እየተመዘገበ ያለውን ሁለንተናዊ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት አጠናክሮ ለማስቀጠል የተጀመሩ የልማት ተግባራት ከዳር እንዲደርሱ ሁላችንም የድርሻችንን ለማበርከት መረባረብ አለብን ብለዋል።

የባሕር ዳር ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ወለላ የኔው እንደገለጹት፤ የመደመር መንግስት መርሆዎች ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና ፋይዳቸው የጎላ ነው።


‎በዚሕም በከተሞች እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎች ከተሞች ፅዱ፣ ሳቢና ማራኪ እንዲሆኑ ከማድረግ ባለፈ ዋነኛ የቱሪዝም መዳረሻ እንዲሆኑ እያስቻለ መሆኑን አንስተዋል።

‎‎በተለይ በባሕርዳር ከተማ የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ስራዎች ባሕርዳር መርጠው የሚጎበኟት የቱሪዝም መዳረሻ ከተማ እንድትሆን ማስቻሉን ገልጸዋል።

‎በቀጣይም በተተኳሪ የልማት መስኮች የተጀመረው የልማት ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከመንግስት ጎን በመሆን የድርሻቸውን ለማበርከት ዝግጁ እንደሆኑም አረጋግጠዋል።

‎‎‎በመደመር መንግስት እይታ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በማዕድን፣ በቱሪዝምና በከተማ መሰረተ ልማት ዘርፎች እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ተግባራትን መንግስት ትኩረት ሰጥቶ እያከናወነ እንደሚገኝ ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026