🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 30/2018 (ኢዜአ)፦ የመደመር መንግስት ከዲጂታል ተደራሽነት ወደ ጋራ ብልፅግና የተጀመረውን ጉዞ ለማሳካት፣ በመፍጠር፣ በመፍጠን እና በእመርታ መርሕ በትጋት እንደሚሰራ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ዲጂታል ኢኮኖሚን መገንባት ምርጫ ሳይሆን ብልጫ ነው! በሚል ርዕስ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ዛሬ ሁለተኛውን የኢትዮጵያ ዲጂታል ክፍያ ጉባኤን በይፋ ማስጀመራቸውን ገልጸዋል።
ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን በውጤታማነት መተግበሩ፣ ለዜጎች ፈጣን፣ ቀልጣፋ እና ወጪ ቆጣቢ አገልግሎቶችን ተደራሽ ከማድረግ ባሻገር፣ የዕለት ከዕለት የኑሮ እንቅስቃሴን እያቀለለ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በተጨማሪም የኤሌክትሮኒክና የዲጂታል ግብይት ሥርዓትን ተመራጭ የክፍያ መንገድ እንዲሆን ማስቻሉን አመልክተዋል።
ይሄም የሕዝብን ኑሮና የመንግሥትን አገልግሎት ከምርጫም በላይ ብልጫ ያለው እንዲሆን ያስችላል ነው ያሉት።
ባለፉት አምስት ዓመታት በተዘረጋው የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት ውስጥ፣ በየዓመቱ ከ18.5 ትሪሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ዝውውር እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
ይሄንን ስኬት በላቀ መልኩ በማስቀጠል ሁሉን አቀፍ ብልፅግናን የማሳካት ግብ የያዘውን የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን በቅርቡ በሚኒስትሮች ምክር ቤት መጽደቁን አውስተዋል።
ስትራቴጂው ዲጂታል መሠረተ ልማትን የማጠናከር፣ ተደራሽነትን ብቻ ሳይሆን አጠቃቀምን ለማስፋት ክሂሎትን የመገንባት እና ችግር ፈቺ ፈጠራን የማበረታታት ዓላማ ያለው መሆኑን ጠቅሰው ለስኬታማነቱ ሁሉም ሚናውን ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመደመር መንግሥት ከዲጂታል ተደራሽነት ወደ ጋራ ብልፅግና የጀመርነውን ጉዞ ለማሳካት፣ በመፍጠር፣ በመፍጠን እና በእመርታ መርሕ ይተጋል ሲሉም ገልጸዋል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026