የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በዲጂታል መታወቂያ ላይ ያለውን የማንነት መረጃ መጠበቅ የሚያስችል የዲጂታል ሰርተፍኬት አገልግሎት ይፋ ሆነ

Dec 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 30/2018(ኢዜአ)፦የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በዲጂታል መታወቂያ ላይ ያለውን የማንነት መረጃ መጠበቅ የሚያስችል የዲጂታል ሰርተፍኬት አገልግሎትን በይፋ አስጀምሯል።

አገልግሎቱ በይፋዊ ቁልፍ መሰረተ ልማት ውስጥ የፋይዳ ደህንነት ማስጠበቂያ ቁልፎች የሚፈጠሩበትና የሚንቀሳቀሱበትን አሰራር ያካተተ ነው ተብሏል።


እነዚህ ቁልፎች በዲጂታል መታወቂያ ላይ ያለውን የማንነት መረጃ ለመጠበቅ ጥቅም ላይ የሚውል የመተማመኛ ዲጂታል ፊርማ ለማዘጋጀት የሚውሉ መሆኑም ተገልጿል።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ፤ ከዚህ ቀደም ለኤሌክትሮኒክ ፓስፖርት የዲጂታል ሰርተፊኬት አገልግሎት መጀመሩን ገልጸው፤ ዛሬ በይፋ የተጀመረው የፋይዳ መታወቂያ ሰርተፊኬት አገልግሎት ቀጣይ ስራ ነው ብለዋል።

የሰርተፊኬት አገልግሎቱ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በከፍተኛ የደህንነት ደረጃዎች ባላቸው ቴክኖሎጂዎች የተጠበቀ እንዲሆን ያግዛል ነው ያሉት።

የማንነት ስርቆትን ለመከላከል፣ማጭበርበር እና የማንነት መረጃን አላግባብ መጠቀምን ለመከላከል የሚያስችል መሆኑንም አመልክተዋል።

ደህንነቱ የተጠበቀ ዲጂታል መታወቂያ ጤና፣ ትምህርት፣ ባንክን ጨምሮ ሌሎች አገልግሎቶች በተሻለ መልኩ ለማግኘት ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው መሆኑም ነው የተገለጹት።

የፋይዳን ደህንነት ማረጋገጥ ደህንነቱ የተጠበቀ አገልግሎት ተደራሽ በማድረግ የተሳለጠ አገልግሎት እንዲኖር ዓይነተኛ ሚና እንደሚጫወት ጠቁመዋል።


የኢትዮጵያ ብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና አስተባባሪ ዮዳሄ አርአያሥላሴ በበኩላቸው፤ 29 ሚሊዮን ዜጎች የፋይዳ መታወቂያ መመዝገባቸውን ተናግረዋል።

መታወቂያ ተደራሽ ከማድረግ ባለፈ ደህንነቱን ማስጠበቅ ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፤ ከዚህ አኳያ የሰርተፊኬት አገልግሎቱ መጀመር ትልቅ እርምጃ ነው ብለዋል።

የሰርተፊኬት አገልግሎቱ የፋይዳ ዲጂታል ሰነዶች ተዓማኒነትን የሚጨምር መሆኑንም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026