🔇Unmute
ወራቤ፤ ታኅሣስ 30/2018(ኢዜአ)፦ በወራቤ ከተማ ከዘጠኝ ሄክታር መሬት በላይ የሚሸፍን የወንዝ ዳርቻ የኮሪደር ልማት ሥራ እየተፋጠነ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ያሲን ከሊል ገለጹ፡፡
ከንቲባው ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ከተማዋን ውብ፣ ፅዱ እንዲሁም ለኑሮ እና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት በልዩ ትኩረት እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡

ከዚህም ውስጥ አንዱ የወንዝ ዳርቻ ልማት መሆኑን ጠቅሰው በከተማ አስተዳደሩና በህብረተሰቡ ተሳትፎ ከ9 ሄክታር በላይ የሚሸፍን የወንዝ ዳርቻ ልማት ግንባታ እየተፋጠነ መሆኑን ተናግረዋል።

የወንዝ ዳርቻ የኮሪደር ልማት ሥራው የከተማውን ገፅታ ከመቀየር ባለፈ ምቹ የመኖሪያ አካባቢ እየፈጠረ መሆኑን ጠቅሰው የልማት ስራውን በሚቀጥሉት ሁለት ወራት ውስጥ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
ከልማት ሥራው በተጨማሪ የመሰብሰቢያ አዳራሽ፣ ካፍቴሪያ፣ የቅርጫትና የመረብ ኳስ መጫወቻ ሜዳ ፋውንቴን እንዲሁም ሰው ሰራሽ አነስተኛ ሐይቅ ማካተቱን ጠቅሰው የእነዚህ ግንባታዎች ስራም እየተጠናቀቀ መሆኑን ጠቁመዋል።
ከ2 ሺህ 500 በላይ ሰዎችን መያዝ የሚችል ቲያትር አዳራሽ፣ የእግር ኳስ ሜዳና ሌሎች የግንባታ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል፡፡

ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ወጣት አብዲ ዋሴ እና አቶ ሸርፈዲን ሹሜ፤ የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራው የወራቤ ከተማን ለነዋሪው ምቹ እንድትሆን ከማድረግ በተጨማሪ ከሌሎች አቻ ከተሞች ጋር ተወዳዳሪ እንደሚያደርጋት ተናግረዋል።
በተለይም በከተማዋ የወንዝ ዳርቻን ለማልማት የተጀመረው ሥራ አካባቢው ቀድሞ የነበረውን መጥፎ ገጽታ በመቀየር ለመዝናኛና ለሥራ ዕድል እንዲውል መደረጉን ገልጸዋል።

በከተማዋ እየታየ ያለው ለውጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥል እያደረግን ያለውን ድጋፍ አጠናክረን እንቀጥላለን ነው ያሉት ነዋሪዎቹ።
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...
Apr 14, 2026
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026