🔇Unmute
ኢትዮጵያ ዘመናዊነት መላበስ በጀመረችበት ወቅት ለህዝብ አገልግሎት እንዲሰጡ ከተቋቋሙ ቀደምት ተቋማት መካከል አንዱ ነው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፡፡
አገልግሎቱ አሰራሩን ሊያቀላጥፉ የሚችሉ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀምና የደንበኞችን እርካታ መጨመር ባለመቻሉ በተደጋጋሚ ቅሬታ ሲያስተናግድ ቆይቷል።
በለውጡ ዓመታት በኢትዮጵያ ዘመናዊ፣ ዘመን ተሻጋሪና ጠንካራ የመንግሥት የአገልግሎት ሥርዓት መዘርጋት የሚያስችል ሪፎርም መካሄዱ ይታወቃል።
የመንግስት አገልግሎቶችን በቴክኖሎጂ በማዘመን ፈጣን፣ ቀልጣፋ እና ከብልሹ አሰራር ለማጽዳት የተጀመረው ጥረት ሕብረተሰቡ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ እርካታ እንዲኖረው እያደረገ ይገኛል።
ዲጂታል ኢትዮጵያን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ኤሌክትሪክ ወሳኝ እንደመሆኑ አገልግሎቱ ለዚህ አስቻይ ሁኔታን ሊፈጥሩ የሚችሉ አሰራሮችን መተግበር ግድ ይለዋል።
አገልግሎቱ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የኤሌክትሪክ ሽፋንን ለማሳደግ የጀመራቸው ሥራዎች ውጤታማ እየሆኑ ይገኛሉ።
ነገር ግን ዲጂታል ኢትዮጵያን ለመገንባት የተያዘው ግብ እውን እንዲሆን ተቋሙን ማዘመን ወሳኝ ጉዳይ ነው።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ኢንጂነር ጌቱ ገረመው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አሁን ካለው ዓለም አቀፋዊ ነባራዊ ሁኔታ አንጻር አሰራርን ከማዘመንና ቴክኖሎጂን ከመጠቀም ውጪ በቀደመው አሰራር ሀገርን ማሻገር አይቻልም ብለዋል።
ይህን ተከትሎ አገልግሎቱ አሰራሩን በቴክኖሎጂ የታገዘ ማድረግ፣ ልምድ ካላቸው ተቋማት ጋር በጋራ መስራት እንዲሁም የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን ለቴክኖሎጂ ምቹ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ይህም በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የተያዙ ግቦች እውን እንዲሆኑ ከፍተኛ እገዛ እንዳለው ነው ያስረዱት።
ዋና ሥራ አሥፈጻሚው እንደሚሉት ተቋማቸው ዘመኑን የዋጀ ቴክኖሎጂ በመጠቀም የደንበኞችን እርካታ የሚጨምሩ አሰራሮችን ተግባራዊ ማድረግ ጀምሯል።
ለአብነት የደንበኞችን እንግልት ለመቀነስና ተገልጋዮች ባሉበት ሆነው የአገልግሎት ክፍያቸውን የሚፈጽሙበት አሰራር ተግባራዊ ማድረጉን ገልጸዋል።
አገልግሎቱ ከመልካም አስተዳደርና ከሙስና ጋር ተያይዞ ተደጋጋሚ ቅሬታ ሲነሳበት እንደነበር አስታውሰውም የጥቆማ አቀባበሉን በማዘመን ለቅሬታዎች ፈጣን ምላሽ መስጠት ተጀምሯል ብለዋል።
ተቋሙ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ወስጥ ዘመናዊና የደንበኞችን ፍላጎት የሚያረካ እንዲሆን የጀመራቸውን ሥራዎች የበለጠ እንደሚያጠናክርም አረጋግጠዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026