የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ኢትዮጵያን በአቪዬሽን ዘርፍ ተወዳዳሪ ማድረግ የሚያስችል አቅም እየተገነባ ነው - ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር)

Jan 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያን በአቪዬሽን ዘርፍ ተወዳዳሪ ማድረግ የሚያስችል አቅም እየተገነባ መሆኑን የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር) ገለጹ።

የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ለሁለት ተቋማት የስራ ፈቃድ ሰጥቷል።

የስራ ፈቃዱ የተሰጠው በአውሮፕላን ጥገና ዘርፍ በኢትዮጵያ አየር ሃይል ውስጥ ለተቋቋመው እና ለግል አየር መንገዶች ጥገና ለሚሰጠው ተቋም ነው።

ባለስልጣኑ በተመሳሳይ ለዓለም አቀፍ የካርጎ አቪዬሽን አገልግሎት ደግሞ የአቪዬሽን ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት የስራ ፈቃድ ሰጥቷል።


የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያን የበረራ ትራንስፖርት (አቪዬሽን) ማዕከል ለማድረግ የተለያዩ የለውጥ እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው፡፡

በዚህም በዘርፉ የኢትዮጵያን ተወዳዳሪነት የሚያሳድግ አቅም እየተገነባ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ግንባታውን በይፋ ያስጀመሩት የቢሾፍቱ ዓለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር መሆኑንም ገልጸዋል፡።

በዛሬው ዕለትም ለሁለቱ ተቋማት የተሰጠው የስራ ፈቃድ በአቪዬሽን ኢንዱስትሪው ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን አንስተዋል፡፡

ለኢትዮጵያ አየር ሃይል በጥገና ዘርፍ የተሰጠው የስራ ፈቃድ የግል አየር መንገዶች ለአውሮፕላን ጥገና የሚያወጡትን ወጪ በከፍተኛ ደረጃ መቀነስ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

በተመሳሳይ የዓለም አቀፍ ካርጎ አቪዬሽን አገልግሎት የአቪዬሽን ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ፈቃድ ማግኘቱ በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ሃይል ለማፍራት በሚደረገው ሀገራዊ ጉዞ ትርጉም ያለው ሚና እንደሚኖረው አስታውቀዋል።

ማሰልጠኛው ከኢትዮጵያ አልፎ በአህጉር ደረጃ ባለሙያዎችን ለማፍራት ለሚደረገው እንቅስቃሴ አዎንታዊ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።


የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዮሃንስ አበራ በበኩላቸው፤ ለተቋማቱ እውቅና የተሰጠው አስፈላጊውን መስፈርት ማሟላታቸው ተረጋግጦ መሆኑን ተናግረዋል።

በስነ-ስርዓቱ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር)፣ የኢፌዴሪ የአየር ሃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳን ጨምሮ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026