የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ያካተቱ የተሽከርካሪ ታርጋዎችን ሥራ ላይ ሊያውል ነው

Jan 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አሁን እየተጠቀመበት ያለውን የተሽከርካሪ ታርጋ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ባካተተ አዲስ ታርጋ ሊቀይር መሆኑን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አዛዥ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል አስታወቁ።

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወር የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ አካሂዷል።


የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አዛዥ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል እንደተናገሩት ፖሊስ አሁን እየተጠቀመባቸው ያሉ የተሽከርካሪ ታርጋዎችን ሙሉ በሙሉ በመቀየር አዳዲስና ዘመናዊ ታርጋዎችን በቅርቡ ስራ ላይ ለማዋል ዝግጅት ማጠናቀቁን ተናግረዋል።

ይህም ተቋሙ የወንጀል መከላከልና ምርመራ ስራውን በዘመናዊ መንገድ ለመምራት ከጀመራቸው የሪፎርም ስራዎች አንዱ መሆኑን ተናግረዋል።


አዲሱ ታርጋ የረቀቁ የቴክኖሎጂ ቁልፎች ያሉት ሲሆን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስን ብቻ የሚወክል፣ የተቋሙን የሙያ ብቃት እንዲሁም የዲሲፕሊን ደረጃ የሚያንፀባርቅ መሆኑን ገልጸዋል።

ኮሚሽነር ጀነራሉ አዲሱ ታርጋ ታትሞ በሚቀጥሉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ በይፋ ጥቅም ላይ እንደሚውል አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.