የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የሴቶችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ለማሳደግ ያግዛል

Jan 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሰመራ፤ ጥር 6/2018(ኢዜአ)፦ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የሴቶችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማሳደግ እንደሚያግዝ የአፋር ክልል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ፋጡማ መሐመድ ተናገሩ።

"ፋይዳ ለሴቶች" በሚል መሪ ሐሳብ በአፋር ክልል የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ የንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል።


በመድረኩ የተገኙት የአፋር ክልል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ፋጡማ መሐመድ እንዳሉት፤ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ለማሳደግ ያለው ሚና ከፍተኛ ነው።

በተለይም ሴቶች በፋይናንሱ ዘርፍ እና በዲጂታል የአገልግሎት አሰጣጥ የሚኖራቸው ተሳትፎ እንዲያድግና ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያበረክተው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።

ንቅናቄውን ተከትሎ እንደ አፋር ክልል በተያዘው ዓመት አንድ ሚሊዮን ሴቶች ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ እንዲኖራቸው እየተሰራ ነው ብለዋል።


የንቅናቄ ስራው በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች እስከታች ድረስ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀው፤ በዚህ ረገድ ለተያዘው ዕቅድ ስኬታማነት የሀገር ሸማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር ፅህፈት ቤት ኀላፊ አቶ አሚን መሐመድ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በተለይም የሴቶችን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው።


የዲጂታል መታወቂያ አገልግሎቱን በተቀላጠፈ ሁኔታ ተደራሽ ለማድረግ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል።

ሴቶች ተደራጅተው የተለያዩ አገልግሎቶችን ለማግኘትም ሆነ በተለያዩ ሥራዎች ውስጥ በመሳተፍ ተጠቃሚ ለመሆን ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ያለው አበርክቶ ላቅ ያለ መሆኑንም አስረድተዋል።

የተጀመረውን የንቅናቄ ተግባሩ እንዲጠናከር በማድረግ በክልል ደረጃ የተያዘው ዕቅድ እንዲሳካ በቁርጠኝነት ይሰራል ብለዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ ከሰመራ ሎጊያ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች፣ ከተለያዩ ማህበራት፣ ከሴቶች አዳሪ ትምህርት ቤትና ከሰመራ ዩኒቨርሲቲ የመጡ ሴቶች ተገኝተው ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያውን ለማግኘት ተመዝግበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.