🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ የካቲት 2/2018(ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) በ39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ሰላም እና የውሃ ሀብቶችን ጨምሮ ቀጣናዊ የትኩረት መስኮች ላይ ትኩረት ያደረገ ተሳትፎ እንደሚኖረው አስታወቀ።
የህብረቱ ጉባኤ የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በመል መሪ ሐሳብ በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል።
ቀደም ብሎ የካቲት 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም 48ኛው የህብረቱ የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ይካሄዳል።
በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ የተመራ ልዑክ በጉባኤው ላይ ይሳተፋል።
ኢጋድ በቀጣናው ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች በአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ይዞ እንደሚቀርብ አስታውቋል።
ሰላም እና ደህንነት፣ የአየር ንብረት፣ የውሃ ሀብቶች እና ቀጣናዊ ትስስር ከአጀንዳዎቹ መካከል በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው።
ኢጋድ በጉባኤው የሚኖረው ተሳትፎ ከቀጣናዊ አጀንዳዎች እና ከአጀንዳ 2063 ግቦች ጋር የተቆራኙ መሆናቸውን አመልክቷል።
በዋና ጸሀፊው የሚመራው ልዑክ ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን፣ ከህብረቱ አባል ሀገራት ጋር በተለያዩ ቀጣናዊ እና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ እንደሚመክር ተመላክቷል።
ኢጋድ የቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች የቅንጅት እና የትብብር ማዕቀፍ ሊቀ መንበርነት በጉባኤው ላይ ለደቡባዊ አፍሪካ ልማት ትብብር ኮንፈረንስ(ሳዴክ) ያስረክባል።
ይህም ለአህጉራዊ ትብብር ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ ገልጿል።
በሚኖሩት ምክክሮች እና ውይይቶች ኢጋድ የአፍሪካ ቀንድ የትኩረት መስኮችን ወደ አህጉራዊው መድረክ በማምጣት የሰላም፣ አይበገሬነትና የጋራ ብልጽግና አጀንዳዎች ለማሳለጥ እንደሚሰራ መግለጹን ኢዜአ ከተቋሙ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
Jul 17, 2025
Apr 24, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፦ የሲሚንቶ ንግድ እና መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎችን በተመለከተ የወጡ መመሪያዎች ገበያውን በማረጋጋትና የዋጋ ግሽበትን በመቀ...
Feb 12, 2025