የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የግብርና አገልግሎቶችን ከዲጂታል መታወቂያ ጋር የማስተሳሰር ተግባር እየተከናወነ ነው

Mar 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ቦንጋ፣ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የግብርና አገልግሎቶችን የማዘመንና ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጋር የማስተሳሰር ተግባር እየተከናወነ መሆኑ ተገለጸ።

በደቡብ ኦሞ ዞን የሚገኙ እምቅ ሃብቶችን በሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር በማገዝ የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ መስራት ይገባል

የክልሉ ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር “ዲጂታል ማንነት ለተረጋገጠ ይዞታ ባለቤትነትና ለላቀ የፋይናንስ ተጠቃሚነት!'' በሚል መሪ ሀሳብ ያዘጋጀው የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ የንቅናቄ መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው የንቅናቄ መድረኩን ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለፁት፤ ዲጂታል ኢትዮጵያን ለመገንባት በሚደረገው እንቅስቃሴ ውስጥ የፋይዳ መታወቂያን ማዳረስ አንዱ ነው።


በአሁኑ ወቅትም የገጠር ትራንፎርሜሽንን እውን ለማድረግ ፈጣንና ዘመናዊ የግብርና አገልግሎቶችን ለአርሶና አርብቶ አደሩ መስጠት እንዲቻል እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።ለዚህም የፋይዳ መታወቂያን የማዳረስ ስራ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

የግብርና አገልግሎቶችን በማዘመን ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጋር ማስተሳሰር የአርሶና አርብቶ አደሩን የብድርና የፋይናንስ ተጠቃሚነት ችግር ለመፍታት እንደሚያስችልም ነው የገለጹት።

ይህም አርሶና አርብቶ አደሩ ባለው እሴት ላይ ተመርኩዞ የፋይናንስ ተጠቃሚ እንዲሆን እንደሚያግዘው ነው የተናገሩት።

የአርሶና አርብቶ አደሩ ዋነኛ ሀብት የሆነውን የመሬት ልኬትን ከሀገራዊ መረጃ ስርዓት ጋር በማቆራኘትና ከዲጂታል መታወቂያ ጋር በማስተሳሰር የፋይናንስ ተደራሽነትን የማረጋገጥ ተግባር እየተከናወነ መሆኑንም አብራርተዋል።

በክልሉ በከተማና በገጠር ከ682 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ለማድረግ መቻሉንም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026