🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ የካቲት 23/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት ሂደት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበ መምጣቱን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ።
የብሔራዊ የአምራች ኢንዱስትሪ ካውንስል በኦሮሚያ ክልል ሸገር፣ ቢሾፍቱ እና አዳማ ከተሞች የሚገኙ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ትናንት እና ዛሬ የመስክ ምልከታ አድርጓል።

ምልከታው የሀገሪቱን የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ አቅም ለመገምገም እና በዘርፉ የሚታዩ ማነቆዎችን ለመለየት ያለመ ነው።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል በጉብኝቱ ማጠናቀቂያ ላይ እንደገለጹት፤ በሦስቱ ከተሞች የታዩት እንቅስቃሴዎች ኢትዮጵያ በዘርፉ የጀመረችው ጉዞ ተስፋ ሰጪ መሆኑን የሚያሳዩ ናቸው።
በጉብኝቱ ወቅት ገቢ ምርቶችን በመተካት፣ የወጪ ምርትን በመጨመር እና ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ ትልልቅ አቅም ያላቸው ኢንዱስትሪዎች መኖራቸውን ማረጋገጥ ተችሏል ብለዋል።
በተለይም የብረታ ብረት፣ የኮንስትራክሽን ሴራሚክ ምርቶች፣ የፋርማሲዩቲካል ምርቶች፣ የምግብ እና ምግብ ነክ ኢንዱስትሪዎች የሚታየው እንቅስቃሴ የሚበረታታ መሆኑ ጠቅሰዋል።
ካውንስሉ ከተቋቋመባቸው ዋና ዓላማዎች አንዱ የመንግስት ድጋፍ በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ መገምገም እንደሆነ የጠቀሱት ሚኒስትሩ፤ በየደረጃው ያለው የመንግስት መዋቅር አምራቾችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን በተግባር ማየታቸውን ገልጸዋል።

መሬት በማቅረብ፣ መሠረተ ልማት በማሟላት እና የግብዓት ችግሮችን በመፍታት ረገድ የተሰሩ ሥራዎች ለአምራቾች ትልቅ የመተማመን መንፈስ የሚፈጥሩ ናቸው ብለዋል።
ኢንዱስትሪዎች አሁን ካሉበት አቅም በላይ እንዲያድጉ እና የማምረት አቅማቸው እንዲጨምር የተለያዩ ተግባራት እንደሚቀሩ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
በክልሉ የታዩት አዳዲስ ፕሮጀክቶች እና ነባር ፋብሪካዎች ኢትዮጵያ በኢንዱስትሪ ላይ የተመሰረተ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት የያዘችውን ራዕይ እውን ለማድረግ የሚያስችሉ መሆናቸውን ካውንስሉ አረጋግጧል ብለዋል።
Jul 17, 2025
Apr 24, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፦ የሲሚንቶ ንግድ እና መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎችን በተመለከተ የወጡ መመሪያዎች ገበያውን በማረጋጋትና የዋጋ ግሽበትን በመቀ...
Feb 12, 2025