🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 1/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት ሰባት አመታት (ከ2010 - 2017 ዓ.ም) በፊስካል ፖሊሲና በመንግስት ፋይናንስ ረገድ ስኬቶች መመዝገባቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ።
ሚኒስቴሩ እንዳመለከተው የመንግሥት የበጀት ጉድለትን ለመቀነስ በተወሰደው ርምጃ ከሀገር ውስጥ ጠቅላላ ምርት -2 ነጥብ 5 በመቶ የነበረው የበጀት ጉድለት ወደ -0 ነጥብ 9 በመቶ ዝቅ ብሏል።
የመንግስትን ገቢ የሚያሻሽሉ ሪፎርሞች ተግባራዊ በመደረጋቸው ጠቅላላ ገቢው ከ5 እጥፍ በላይ አድጓል።

የመንግስት የወጪ አቅጣጫው ድህነትን ለመዋጋትና ልማትን ለማረጋገጥ እንዲውል በመደረጉም ድህነት ተኮር ወጪ ከ5 እጥፍ በላይ አድጓል።
የበጀት ተዓማኒነትን ለማረጋገጥ የሚያግዝ የመካከለኛ ዘመን የፊስካል ማዕቀፍ እንዲጠናከር በመደረጉ የበጀት አፈጻጸሙ ተሻሽሏል።
ከብሔራዊ ባንክ የሚወሰደው ቀጥታ ብድር እንዲቀር በመደረጉ የዋጋ ንረትን ለመግታት አስተዋጽኦ አድርጓል።
መንግሥት የተቀናጀ የፋይናንስ አስተዳደር የመረጃ ስርዓት መዘርጋቱን ገልጾ፤ የዲጂታል ክፍያ አማራጮችን በመተግበር የፋይናንስ ስርዓቶችን በማዘመን የፋይናንስ አስተዳደር ስርዓት ማዘመን እንደተቻለ ገልጿል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026