🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 1/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት ሰባት አመታት (ከ2010 - 2017 ዓ.ም) በፊስካል ፖሊሲና በመንግስት ፋይናንስ ረገድ ስኬቶች መመዝገባቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ።
ሚኒስቴሩ እንዳመለከተው የመንግሥት የበጀት ጉድለትን ለመቀነስ በተወሰደው ርምጃ ከሀገር ውስጥ ጠቅላላ ምርት -2 ነጥብ 5 በመቶ የነበረው የበጀት ጉድለት ወደ -0 ነጥብ 9 በመቶ ዝቅ ብሏል።
የመንግስትን ገቢ የሚያሻሽሉ ሪፎርሞች ተግባራዊ በመደረጋቸው ጠቅላላ ገቢው ከ5 እጥፍ በላይ አድጓል።

የመንግስት የወጪ አቅጣጫው ድህነትን ለመዋጋትና ልማትን ለማረጋገጥ እንዲውል በመደረጉም ድህነት ተኮር ወጪ ከ5 እጥፍ በላይ አድጓል።
የበጀት ተዓማኒነትን ለማረጋገጥ የሚያግዝ የመካከለኛ ዘመን የፊስካል ማዕቀፍ እንዲጠናከር በመደረጉ የበጀት አፈጻጸሙ ተሻሽሏል።
ከብሔራዊ ባንክ የሚወሰደው ቀጥታ ብድር እንዲቀር በመደረጉ የዋጋ ንረትን ለመግታት አስተዋጽኦ አድርጓል።
መንግሥት የተቀናጀ የፋይናንስ አስተዳደር የመረጃ ስርዓት መዘርጋቱን ገልጾ፤ የዲጂታል ክፍያ አማራጮችን በመተግበር የፋይናንስ ስርዓቶችን በማዘመን የፋይናንስ አስተዳደር ስርዓት ማዘመን እንደተቻለ ገልጿል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026