የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ነዳጅን በቁጠባ እንጠቀም - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Mar 19, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 10/2018(ኢዜአ)፦ የመዲናዋ ነዋሪዎች ነዳጅን በቁጠባ በመጠቀም ትብብር እንዲያደርጉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ጥሪ አቀረቡ።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት በአሁኑ ወቅት በመካከለኛው ምሥራቅ በተፈጠረው ቀውስ ምክንያት፣ ኢትዮጵያን ጨምሮ ነዳጅ ገዝተው የሚጠቀሙ ሀገራት አቅርቦቱን እንደልብ ለማግኘት መቸገራቸውን ገልጸዋል።

ችግሩ ተፈትቶ የነዳጅ አቅርቦት ሥርዓት ወደ መደበኛ ሁኔታ እስኪመለስ ድረስ ነዳጅን በቁጠባ መጠቀም እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

ስለሆነም የከተማዋ ነዋሪዎች አጫጭር መንገዶችን በእግር በመጓዝ፣ እንዲሁም የብስክሌት አማራጮችን እና የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በመጠቀም ትብብር እንዲያደርጉ ከንቲባዋ ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.