የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በመጪው ክረምት የሚተከሉ የተሻሻሉ የቡና ችግኞች ዝግጅት እየተከናወነ ነው

Mar 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጊምቢ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፦ በምዕራብ ወለጋ ዞን በመጪው ክረምት የሚተከሉ የተሻሻሉ የቡና ችግኞች ዝግጅት በስፋት እየተካሄደ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ ፈይሳ ሀምቢሳ አስታወቁ።


የቡና ችግኙ በሦስት ዓመት ውስጥ ምርት መስጠት የሚችል መሆኑን ጠቁመው፤ በሔክታር እስከ 12 ኩንታል ምርት እንደሚያስገኝ ለኢዜአ አረጋግጠዋል።

በአሁኑ ወቅትም ከ370 ሚሊየን በላይ ችግኞች መዘጋጀታቸውን እና ለተከላ የሚውል የጉድጓድ ቁፋሮን ጨምሮ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት እየተከናወነ ነው ብለዋል።

የተሻሻሉት ችግኞች የቡና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ ባለፈ፤ ከቡና የሚገኘውን የውጭ ምንዛሬ ለማሳደግ ጉልኅ አስተዋጽኦ እንደሚኖራቸው አስረድተዋል።

በሌላ በኩል ከ66 ሺህ ሔክታር በሚልቅ መሬት ላይ የሚገኝና ምርት የማይሰጥ ያረጀ ቡናን የመንቀል ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026