🔇Unmute
ጊምቢ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፦ በምዕራብ ወለጋ ዞን በመጪው ክረምት የሚተከሉ የተሻሻሉ የቡና ችግኞች ዝግጅት በስፋት እየተካሄደ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ ፈይሳ ሀምቢሳ አስታወቁ።

የቡና ችግኙ በሦስት ዓመት ውስጥ ምርት መስጠት የሚችል መሆኑን ጠቁመው፤ በሔክታር እስከ 12 ኩንታል ምርት እንደሚያስገኝ ለኢዜአ አረጋግጠዋል።
በአሁኑ ወቅትም ከ370 ሚሊየን በላይ ችግኞች መዘጋጀታቸውን እና ለተከላ የሚውል የጉድጓድ ቁፋሮን ጨምሮ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት እየተከናወነ ነው ብለዋል።
የተሻሻሉት ችግኞች የቡና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ ባለፈ፤ ከቡና የሚገኘውን የውጭ ምንዛሬ ለማሳደግ ጉልኅ አስተዋጽኦ እንደሚኖራቸው አስረድተዋል።
በሌላ በኩል ከ66 ሺህ ሔክታር በሚልቅ መሬት ላይ የሚገኝና ምርት የማይሰጥ ያረጀ ቡናን የመንቀል ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አስታውቀዋል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026