የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በክልሉ የዋጋ ንረትን ለማርገብ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

Mar 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር ፤ መጋቢት 13/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የግብይት ማዕከላትን በማስፋፋትና የንግድ ሰንሰለትን በማሳጠር የዋጋ ንረትን ለማርገብ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ገለጹ።

በአማራ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ እና በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር የበጀት ድጋፍ የተገነባው የባህር ዳር ከተማ 2ኛ ደረጃ ዘመናዊ የገበያ ማዕከል ዛሬ ተመርቋል።


ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት፤ በክልሉ የገበያ ማዕከላትን በማስፋፋት የዋጋ ንረትን ለመከላከል አቅጣጫ ተቀምጦ በትኩረት እየተሰራ ነው።

የገበያ ማዕከላት ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ ግብይት እንዲያካሄድ የሚያስችሉ በመሆናቸው የማስፋፋት ስራ ልዩ ትኩረት የተሰጠው ጉዳይ ነው ሲሉ አክለዋል።

የገበያ ማዕከላት አምራቹንና ሸማቹን ቀጥታ በማገናኘት ከደላላ ጣልቃ ገብነት የጸዳ የግብይት ስርዓት ለማዳበር ሚናቸው የጎላ መሆኑን አመልክተዋል።


በክልሉ በርካታ የግብርና ምርት ማዕከላት እየተገነቡ መሆኑን ገልጸው ተግባሩን አጠናክሮ በማስቀጠል የዋጋ ንረትን የማርገብ ስራ በልዩ ትኩረት ይከናወናል ብለዋል።

በባህር ዳር ከተማ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት በሆነው የገበያ ማዕከል የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቾች እንደሚቀርቡ ታውቋል።

በምረቃ ስነ-ሥርዓቱ ላይ የክልሉና የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር አመራር አካላትና አምራቾች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የማዕድን ሀብት ልማት ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ አቅም እየሆነ ነው

ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...

Jun 10, 2026

የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ የሕዝብን ሀብት ለልማት በማዋል በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...

Jun 9, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...

May 28, 2026

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026