የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የተንዳሆ መስኖ መሠረተ ልማት እስከ 60 ሺህ ሄክታር መሬት የማልማት አቅም አለው

Mar 31, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018(ኢዜአ)፦ የተንዳሆ መስኖ መሠረተ ልማት እስከ 60 ሺህ ሄክታር መሬት የማልማት አቅም እንዳለው የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር) ገለጹ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የተንዳሆ መስኖ ልማት ማጠናቀቂያና መልሶ ግንባታ ፕሮጀክትን መርቀዋል።


በዚሁ ወቅት የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር)፤ ባለፉት ጥቂት ወራት በጠንካራ የፕሮጀክት አመራር አምስት የመስኖ ፕሮጀክቶች ተጠናቅቀው ወደ አገልግሎት መግባታቸውን አንስተዋል።

ይህም በፌዴራል መንግሥት ያላሰለሰ ድጋፍና በክልሎች ቁርጠኝነት የተሳካ ነው ብለዋል።


የተንዳሆ ፕሮጀክት ስኬትም የግብርና ምርታማነት የተስፋ ምንጭና የኢኮኖሚ መሠረት መሆኑን ገልጸዋል።

ፕሮጀክቱ በመጠናቀቁ የአካባቢው አርሶና አርብቶ አደሮች ከዝናብ ጥገኝነት ተላቀው በዓመት እስከ ሦስት ጊዜ በማምረት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ለተጀመረው ጥረት ላቅ ያለ ድርሻ እንዳለው ተናግረዋል።

ፕሮጀክቱ ከ15 ዓመታት በፊት ቢጀመርም የማህበረሰቡ የስጋት ምንጭ ከመሆን ያለፈ ጥቅም ሳይሰጥ መቆየቱን ተናግረዋል።

የውሃ ፍሰቱን መቆጣጠር የሚያስችል ሥርዓት በአግባቡ ስላልተዘረጋለት ተጨማሪ ችግር እንደነበረበትም ጠቅሰዋል።

አሁን ላይም የፕሮጀክቱን ውስብስብ ችግሮች እንዲቃለሉ በማድረግ ወደ ሥራ መግባቱን አንስተዋል።

ባለፉት ጥቂት ዓመታት የግድቡን ሁኔታ በማጥናት የውሃ ማስተንፈሻ ችግሮች እንዲስተካከሉ መደረጉንና 40 ኪሎ ሜትር የካናል ዕድሳት ሥራ መሰራቱን ገልጸዋል።

ማህበረሰቡንና ካናሎቹን ከጎርፍ ለመከላከልም 27 ኪሎ ሜትር የድጋፍ ግንብ መገንባቱን አስታውቀዋል።

የተንዳሆ የመስኖ መሠረተ ልማት 60 ሺህ ሄክታር የማልማት አቅም እንዳለው ጠቅሰው፤ በአሁኑ ወቅት 33 ሺህ ሄክታር ለማልማት ዝግጁ ሆኗል ብለዋል።

ከዚህ ውስጥም 23 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ የመስኖ ልማቶች መሸፈኑንም ሚኒስትሩ አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.