🔇Unmute
ደሴ፤መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን ከ52 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በበልግ ሰብል መሸፈኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ፡፡
በደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ ይመር ሰይድ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው።
የበልግ ሰብል ልማቱን ለማሳካት የሜካናይዜሽንና የግብአት እቅርቦት በወቅቱ ለአርሶ አደሩ ተደራሽ መደረጉን አንስተዋል።
እየጣለ ያለውን የበልግ ዝናብ በመጠቀም ከ104 ሺህ 600 ሄክታር የሚበልጥ መሬት በማልማት ከ1 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን ገልጸዋል።
እስካሁን በተደረገው ጥረትም ከ52 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች በዘር መሸፈን ጠቁመዋል።
የዘር ሥራውን አጠናክሮ በማስቀጠል እስከ ያዝነው ወር መጨረሻ እቅዱን ሙሉ በሙሉ ለማሳካት አመራሩና ባለሙያው የተጠናከረ ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በዞኑ በኩታበር ወረዳ 03 ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር አህመድ ዳውድ ፤ እየጣለ ያለውን ዝናብ በመጠቀም አንድ ሄክታር የሚጠጋ ማሳቸውን በስንዴና ገብስ ዘር መሸፈናቸውን ተናግረዋል።
ዝናቡ ለሰብል ልማቱ ምቹ በመሆኑ በማሳቸው ላይ የአረምና ተባይን የመከላከል ስራዎችን በማከናወን ከ30 ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
ሌላው የዚሁ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ሰይድ ከበደ በበኩላቸው፤ እየጣለ ያለውን የበልግ ዝናብ ተጠቅመው ያላቸውን ከግማሽ ሄክታር በላይ መሬት በስንዴ እና ገብስ ዘር መሸፈናቸውን ተናግረዋል።
የተሻሻሉ አሰራሮችንና ቴክኖሎጂን በመጠቀም በምግብ ራሴን ከመቻል ባለፈ ትርፍ ምርት በማምረት ለገበያ ለማቅረብ እየሰራሁ ነው ብለዋል።
በደቡብ ወሎ ዞን ባለፈው ዓመት በበልግ ከለማው 60 ሄክታር መሬት ከ360 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን ከዞኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026
Jul 17, 2025
Apr 24, 2025