🔇Unmute
አዲስ አበባ፤መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የጤና ሥርዓቱን የሚያዘምን አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳህረላ አብዱላሂ ገለጹ።
በጤና ሚኒስቴር ብሔራዊ የጤና ኢኖቬሽን ማበልፀግያና በሀርቫርድ ጤና ስርዓት ኢኖቬሽን ሃካቶን ትብብር በአዲስ አበባ የተዘጋጀው የ2026 ዓለም አቀፍ የጤና ኢኖቬሽን ጉባኤ መካሄድ ጀምሯል።

ጉባዔው በኢትዮጵያ ለመጀመርያ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ7ኛ ጊዜ የሚካሄድ ሲሆን "ሰው ሰራሽ አስተውሎት፤ ለላቀ የጤና ሥርዓት ግንባታ" በሚል መሪ ቃል ከዛሬ መጋቢት 25 እስከ 26/2018 ዓ.ም ይቆያል።
በዚሁ ጊዜ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳህረላ አብዱላሂ፤ የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማት የጤና ጥራትና ፍትሐዊ ተደራሽነትን በማጠናከር ከፍተኛ እገዛ እያደረገ ነው ብለዋል።
በዲጂታል ዘርፍ የተወሰዱ የሕግና የአሰራር ማሻሻያዎችም የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓት በማዘመን ተጨባጭ ውጤቶች ማስገኘታቸውን ገልጸዋል።

በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ መነሻነትም ሀገር በቀል የፈጠራ ክህሎትን በማዳበር የጤና ተቋማትን የማዘመን ሥራ ትኩረት እንደተሰጠው አስረድተዋል።
በጤና ሚኒስቴር የዲጂታል ፈጠራ አስቻይ ምኅዳርም የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ መዋቅራዊ የአሰራር ለውጥ እየተደረገ እንደሚገኝ አንስተዋል።
በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዘርፍ የጤና ሥርዓቱን ለማዘመን የሚከናወኑ ተግባራት ውጤታማነትን በማሳደግ ወሳኝ አቅም እየተፈጠረ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የዲጂታል ምኅዳሩን በማስፋት በዕውቀትና ክህሎት የበለጸገ የሰው ሃብት የማፍራት ስራ እየተከናወነ ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓት ለማዘመን በሚደረገው ጥረት የሰው ሰራሽ አስተውሎትን ጥቅም ላይ በማዋል የአገልግሎት ጥራትን በማስጠበቅ የሰውን ህይወት ለመታደግ ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል።
በሀገራዊ ለውጡ ማግስት በዲጂታል ዘርፍ የተመዘገቡ አስደናቂ የዲጂታል ስኬቶችም ኢትዮጵያ ጉባኤውን ለመጀመሪያ ጊዜ እንድታዘጋጅ ማስቻሉን አስረተድዋል።
በጉባኤው ላይ 60 ኢትዮጵያዊያን የጤና ሙያተኞች፣ የሶፍትዌር አልሚዎች፣ ተመራማሪዎችና ተማሪዎች የጤና ሥርዓትን የሚያሻሽሉ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለውድድር እንደሚያቀርቡም አስታውቀዋል።
በቀጣይም የዲጂታል መሰረተ ልማትን በማስፋት የፈጠራና ክህሎት ዝንባሌ ያላቸው ዜጎችን የማብቃት ሥራ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026