🔇Unmute
አሶሳ፤መጋቢት 28/2018 (ኢዜአ)፦በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርናን በማዘመን በተከናወኑ ተግባራት ምርትና ምርታማነት እያደገ መምጣቱን ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ተናገሩ።
10ኛው ክልላዊ የግብርና ልማት አጋር አካላት የግንኙነት ካውንስል ጉባኤ፣የ2017/18 የመኸር ምርት አፈጻጸም እና የ2018/19 የመኸር ምርት ዕቅድ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በአሶሳ ከተማ ተካሂዷል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን እንዳሉት፥ በክልሉ የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን እየተመዘገበ ያለው ለውጥ የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና ከማረጋገጥ ባለፈ የኢኮኖሚ አቅሙን እንዲያሳድግ አድርጓል።
አዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም እየተከናወነ የሚገኘው የግብርና ሥራ ሰፋፊ ማሳዎችን በዘር ከመሸፈን ባለፈ ምርታማነት እንዲጨምር ማድረጉን ተናግረዋል።
በክልሉ በሌማት ትሩፋት፣በአረንጓዴ አሻራ፣በሩዝ፣ በስንዴና በተፋሰስ ልማት እየተከናወኑ የሚገኙ አበረታች ተግባራትን በማጠናከር የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ማሳደግ እንደሚገባ ገልጸዋል።
መንግሥት ለግብርናው ዘርፍ ልዩ ትኩረት በመስጠት ያከናወናቸው የመስኖ ግንባታዎች እና ዘርፉን የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ባበክር ሀሊፋ በበኩላቸው፤ በ2017/18 የመኸር እርሻ 55 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መሰብሰቡን አስታውቀዋል።
በ2018/2019 የመኸር እርሻ በክልሉ 2 ሚሊዮን ሄክታር መሬትን በማልማት ከ70 ሚሊዮን በላይ ኩንታል ምርት ለማግኘት ዕቅድ መያዙን ኃላፊው ገልጸዋል።
በመድረኩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የዘርፉ አመራሮች እና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...
Apr 14, 2026
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026