የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በክልሉ ግብርናን በማዘመን በተከናወኑ ተግባራት ምርትና ምርታማነት እያደገ መጥቷል-ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን

Apr 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤መጋቢት 28/2018 (ኢዜአ)፦በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርናን በማዘመን በተከናወኑ ተግባራት ምርትና ምርታማነት እያደገ መምጣቱን ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ተናገሩ።

10ኛው ክልላዊ የግብርና ልማት አጋር አካላት የግንኙነት ካውንስል ጉባኤ፣የ2017/18 የመኸር ምርት አፈጻጸም እና የ2018/19 የመኸር ምርት ዕቅድ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በአሶሳ ከተማ ተካሂዷል።


በመድረኩ ላይ የተገኙት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን እንዳሉት፥ በክልሉ የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን እየተመዘገበ ያለው ለውጥ የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና ከማረጋገጥ ባለፈ የኢኮኖሚ አቅሙን እንዲያሳድግ አድርጓል።

አዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም እየተከናወነ የሚገኘው የግብርና ሥራ ሰፋፊ ማሳዎችን በዘር ከመሸፈን ባለፈ ምርታማነት እንዲጨምር ማድረጉን ተናግረዋል።

በክልሉ በሌማት ትሩፋት፣በአረንጓዴ አሻራ፣በሩዝ፣ በስንዴና በተፋሰስ ልማት እየተከናወኑ የሚገኙ አበረታች ተግባራትን በማጠናከር የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ማሳደግ እንደሚገባ ገልጸዋል።

መንግሥት ለግብርናው ዘርፍ ልዩ ትኩረት በመስጠት ያከናወናቸው የመስኖ ግንባታዎች እና ዘርፉን የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸዋል።


የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ባበክር ሀሊፋ በበኩላቸው፤ በ2017/18 የመኸር እርሻ 55 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መሰብሰቡን አስታውቀዋል።

በ2018/2019 የመኸር እርሻ በክልሉ 2 ሚሊዮን ሄክታር መሬትን በማልማት ከ70 ሚሊዮን በላይ ኩንታል ምርት ለማግኘት ዕቅድ መያዙን ኃላፊው ገልጸዋል።

በመድረኩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የዘርፉ አመራሮች እና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026