የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ምክር ቤቱ የተሻሻለውን የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር አዋጅን አፀደቀ   

Apr 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተሻሻለውን የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር አዋጅን በሙሉ ድምፅ አፀደቀ ።

6ኛው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 14ኛ መደበኛ ስብሰባውን ዛሬ አካሂዷል።

ምክር ቤቱ የምክር ቤቱን 5ኛ አመት የስራ ዘመን 13ኛ መደበኛ ስብሰባ ቃለ ጉባኤን እና የተሻሻለውን የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅን በሚመለከት ከግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የቀረበለትን ሪፖርትና ውሳኔ ሃሳብ መርምሮ አፅድቋል።

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ ሪፖርቱንና የውሳኔ ሃሳቡን ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ለግብርና ዘርፍ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች ትገኛለች።

የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትን ተደራሽነት ለማስፋት፣ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ አዋጅ መዘጋጀቱንም ገልጸዋል።

አዋጁ በዚህ ረገድ የግብርና ቴክኖሎጂን ማስተዋወቅና ጥቅም ላይ ማዋል እንዲሁም የግብርና ቢዝነስን ለማስፋት ወሳኝ መሆኑንም ተናግረዋል።

በሌላ በኩል ምክር ቤቱ የመረጃ ነፃነት ረቂቅ አዋጅን እና የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ለሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴዎች መርቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.