የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ለትንሳኤ በዓል በቂ የእንስሳትና የእንስሳት ተዋጽኦ ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ ለማህበረሰቡ እየቀረበ ነው

Apr 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ ለትንሳኤ በዓል በቂ የእንስሳትና የእንስሳት ተዋጽኦ ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ ለማህበረሰቡ እያቀረበ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አርሶ አደርና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽን ገለጸ።

በመዲናዋ ለመጪው የትንሳኤ በዓል ፍጆታ የሚውሉ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች በስፋት ወደ ገበያ እየቀረቡ ነው።


የአዲስ አበባ ከተማ አርሶ አደርና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽነር ባዩ ሽጉጤ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ለበዓል ፍጆታ በቂ የእንስሳትና የእንስሳት ተዋፅኦ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እያቀረብን ነው ብለዋል።

የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ የገበያ መረጋጋት ለመፍጠርና በኅብረተሰቡ ፍላጎት ልክ በቂ ምርት ለመቅራብ ሰፊ ዝግጅት ማድረጉን አስታወቀዋል።

በተለይ በበዓሉ የተለያዩ የእንስሳት ተዋፅኦ ምርቶችን ህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲሸምት ዝግጅት በማድረግ ወደ ሥራ መግባቱን አንስተዋል፡፡

በዚህም ለበዓሉ ፍጆታ የሚውሉ እንደ እንቁላል፣ ቅቤ፣ አይብ፣ ዶሮና የደለቡ በሬዎች በበቂ ሁኔታ እና በተመጣጣኝ ዋጋ መቅረብ መጀመራቸውን አስታውቀዋል።


እነዚህ ምርቶች በከተማዋ በተዘጋጁ ባዛሮችና ኤግዚቢሽኖች እንዲሁም በእንስሳት ልማትና ልህቀት ማዕከል ስር በሚገኙ ሱቆች ለተጠቃሚው እየቀረቡ መሆኑን ተናግረዋል።

የእንስሳት ልማትና ልህቀት ማዕከል ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አሌክስ ደመቀ በበኩላቸው፤ ማዕከሉ ጥራት ያላቸው ምርቶችን ለኅብረተሰቡ ተደራሽ እያደረገ ነው ብለዋል።


በኤልያስ፣ ይሳቅና ጓደኞቻቸው የወተት ተዋፅኦ ህብረት ስራ ማህበር የሽያጭ ባለሙያ የሆኑት የሺወርቅ ዳኛቸው ለበዓሉ የሚፈለጉ የቅቤና አይብ ምርቶች በስፋት ማቅረባቸውን ተናግረዋል።

ሰላም የዶሮ እርባታ እና የእንቁላል ሽያጭ ሽርክና ማህበር ተወካይ ብርቅነሽ ዳባ እንቁላልን ጨምሮ የበዓል ፍጆታ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እየሸጡ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.