🔇Unmute
ጅማ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በጅማ ከተማ ህገወጥ የነዳጅ ግብይትን የመቆጣጠር ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ።
በከተማዋ ነዳጅ በህገወጥ መንገድ ሲያዘዋውሩ የነበሩ አካላት በቁጥጥር ስር ውለዋል።
የጅማ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የኮሙኒኬሽን ክፍል ሀላፊ ኮማንደር ገዛኸኝ አውግቸው ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በከተማው በነዳጅ ግብይት ህገወጥነትን ለመከላከል ጠንካራ ክትትል እየተደረገ ነው።
በዚህም ትናንት ከለሊቱ ዘጠኝ ሰአት ላይ በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 250 ሊትር ነዳጅ በፀጥታ አካላት ክትትል ተይዟል ብለዋል።

በዚሁ ህገወጥ ተግባር የተጠረጠሩ አምስት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ከዚህ በተጨማሪም መንግስት ያስቀመጠውን የነዳጅ ሽያጭ መመሪያ በመተላለፍ በህገወጥ መንገድ ቤንዚል በመሸጥ ላይ የነበረ አንድ የነዳጅ ማደያ እንዲታሸግ መደረጉን ጠቁመው በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ ምርመራ እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል ።
ማህበረሰቡ ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት የሚንቀሳቀሱ ህገወጥ አካላትን ሲመለከት ለፀጥታ አካላት ጥቆማ በመስጠት ትብብሩን እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026
Jul 17, 2025
Apr 24, 2025