የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በጅማ ከተማ ህገወጥ የነዳጅ ግብይትን የመቆጣጠር ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

Apr 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅማ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በጅማ ከተማ ህገወጥ የነዳጅ ግብይትን የመቆጣጠር ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ።

በከተማዋ ነዳጅ በህገወጥ መንገድ ሲያዘዋውሩ የነበሩ አካላት በቁጥጥር ስር ውለዋል።

የጅማ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የኮሙኒኬሽን ክፍል ሀላፊ ኮማንደር ገዛኸኝ አውግቸው ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በከተማው በነዳጅ ግብይት ህገወጥነትን ለመከላከል ጠንካራ ክትትል እየተደረገ ነው።

በዚህም ትናንት ከለሊቱ ዘጠኝ ሰአት ላይ በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 250 ሊትር ነዳጅ በፀጥታ አካላት ክትትል ተይዟል ብለዋል።


በዚሁ ህገወጥ ተግባር የተጠረጠሩ አምስት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው መሆኑን ተናግረዋል።

ከዚህ በተጨማሪም መንግስት ያስቀመጠውን የነዳጅ ሽያጭ መመሪያ በመተላለፍ በህገወጥ መንገድ ቤንዚል በመሸጥ ላይ የነበረ አንድ የነዳጅ ማደያ እንዲታሸግ መደረጉን ጠቁመው በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ ምርመራ እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል ።

ማህበረሰቡ ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት የሚንቀሳቀሱ ህገወጥ አካላትን ሲመለከት ለፀጥታ አካላት ጥቆማ በመስጠት ትብብሩን እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.