🔇Unmute
ጅማ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በጅማ ከተማ ህገወጥ የነዳጅ ግብይትን የመቆጣጠር ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ።
በከተማዋ ነዳጅ በህገወጥ መንገድ ሲያዘዋውሩ የነበሩ አካላት በቁጥጥር ስር ውለዋል።
የጅማ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የኮሙኒኬሽን ክፍል ሀላፊ ኮማንደር ገዛኸኝ አውግቸው ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በከተማው በነዳጅ ግብይት ህገወጥነትን ለመከላከል ጠንካራ ክትትል እየተደረገ ነው።
በዚህም ትናንት ከለሊቱ ዘጠኝ ሰአት ላይ በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 250 ሊትር ነዳጅ በፀጥታ አካላት ክትትል ተይዟል ብለዋል።

በዚሁ ህገወጥ ተግባር የተጠረጠሩ አምስት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ከዚህ በተጨማሪም መንግስት ያስቀመጠውን የነዳጅ ሽያጭ መመሪያ በመተላለፍ በህገወጥ መንገድ ቤንዚል በመሸጥ ላይ የነበረ አንድ የነዳጅ ማደያ እንዲታሸግ መደረጉን ጠቁመው በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ ምርመራ እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል ።
ማህበረሰቡ ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት የሚንቀሳቀሱ ህገወጥ አካላትን ሲመለከት ለፀጥታ አካላት ጥቆማ በመስጠት ትብብሩን እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026