የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በጅማ ከተማ ህገወጥ የነዳጅ ግብይትን የመቆጣጠር ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

Apr 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅማ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በጅማ ከተማ ህገወጥ የነዳጅ ግብይትን የመቆጣጠር ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ።

በከተማዋ ነዳጅ በህገወጥ መንገድ ሲያዘዋውሩ የነበሩ አካላት በቁጥጥር ስር ውለዋል።

የጅማ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የኮሙኒኬሽን ክፍል ሀላፊ ኮማንደር ገዛኸኝ አውግቸው ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በከተማው በነዳጅ ግብይት ህገወጥነትን ለመከላከል ጠንካራ ክትትል እየተደረገ ነው።

በዚህም ትናንት ከለሊቱ ዘጠኝ ሰአት ላይ በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 250 ሊትር ነዳጅ በፀጥታ አካላት ክትትል ተይዟል ብለዋል።


በዚሁ ህገወጥ ተግባር የተጠረጠሩ አምስት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው መሆኑን ተናግረዋል።

ከዚህ በተጨማሪም መንግስት ያስቀመጠውን የነዳጅ ሽያጭ መመሪያ በመተላለፍ በህገወጥ መንገድ ቤንዚል በመሸጥ ላይ የነበረ አንድ የነዳጅ ማደያ እንዲታሸግ መደረጉን ጠቁመው በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ ምርመራ እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል ።

ማህበረሰቡ ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት የሚንቀሳቀሱ ህገወጥ አካላትን ሲመለከት ለፀጥታ አካላት ጥቆማ በመስጠት ትብብሩን እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026