🔇Unmute
ቢሾፍቱ ፤ ሚያዚያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት በተከናወኑ ተግባራት የሕዝቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ያሳደጉ እና የአገልግሎት አሰጣጥን ያሻሻሉ ስኬቶች መመዝገባቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ገለጹ።
የክልሉ የፓርቲና የመንግሥት የሦስተኛ ሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ በቢሾፍቱ ከተማ በሚገኘው የሀርሰዴ አዳራሽ እየተካሄደ ነው።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በርካታ ስኬታማ የልማትና የብልጽግና ተግባራት ተከናውነዋል።
በተለይም የክልሉን ሕዝብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በተሻለ መልኩ ያሳደጉ የከተማ እና የገጠር የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል።
ከዚህም ባለፈ የክልሉን የልማት ሥራዎች ለማቀላጠፍ የሚያግዙ በቴክኖሎጂ የተደገፉ የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓቶች መተግበራቸውንም ተናግረዋል።
በቀጣይም የተመዘገቡ በጎ ሥራዎችን የበለጠ ከማጠናከር ባለፈ፣ ዕቅዶችን በአግባቡ ካለመተግበር ጋር ተያይዘው የሚታዩ ክፍተቶችን ማረም ይገባል ብለዋል።

በተለይም ሁሉንም የልማት ኃይሎች በማቀናጀት የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ውጤታማ ማድረግ ከክልሉ አመራር የሚጠበቅ መሆኑን አስገንዝበዋል።
በግምገማው ጠንካራ ጎኖችን ለማስቀጠልና በሥራ ላይ ያሉ ማነቆዎችን ለመቅረፍ የሚያስችሉ ዝርዝር አቅጣጫዎች እንደሚቀመጡበትም ገልጸዋል።
በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ከፍያለው ተፈራ በበኩላቸው፤ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በርካታ የልማት ተግባራት መከናወናቸውንና የማኅበረሰቡም ተሳትፎ ጠንካራ እንደነበር ገልጸዋል።

በዘጠኝ ወራቱ በፈተናዎች ውስጥ አልፎ ትልቅ ውጤት መመዝገቡን የተናገሩት ኃላፊው፤ በቀረው አጭር የበጀት ዓመቱ ወራት ውስጥ ያልተከናወኑ ሥራዎችን በላቀ ቁርጠኝነት በማከናወን የማኅበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መሥራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
የመንግስት የማስፈጸም አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን ባለፉት ዘጠኝ ወራት የተከናወኑ ተግባራት የሚያሳዩ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026