🔇Unmute
ቢሾፍቱ ፤ ሚያዚያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት በተከናወኑ ተግባራት የሕዝቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ያሳደጉ እና የአገልግሎት አሰጣጥን ያሻሻሉ ስኬቶች መመዝገባቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ገለጹ።
የክልሉ የፓርቲና የመንግሥት የሦስተኛ ሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ በቢሾፍቱ ከተማ በሚገኘው የሀርሰዴ አዳራሽ እየተካሄደ ነው።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በርካታ ስኬታማ የልማትና የብልጽግና ተግባራት ተከናውነዋል።
በተለይም የክልሉን ሕዝብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በተሻለ መልኩ ያሳደጉ የከተማ እና የገጠር የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል።
ከዚህም ባለፈ የክልሉን የልማት ሥራዎች ለማቀላጠፍ የሚያግዙ በቴክኖሎጂ የተደገፉ የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓቶች መተግበራቸውንም ተናግረዋል።
በቀጣይም የተመዘገቡ በጎ ሥራዎችን የበለጠ ከማጠናከር ባለፈ፣ ዕቅዶችን በአግባቡ ካለመተግበር ጋር ተያይዘው የሚታዩ ክፍተቶችን ማረም ይገባል ብለዋል።

በተለይም ሁሉንም የልማት ኃይሎች በማቀናጀት የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ውጤታማ ማድረግ ከክልሉ አመራር የሚጠበቅ መሆኑን አስገንዝበዋል።
በግምገማው ጠንካራ ጎኖችን ለማስቀጠልና በሥራ ላይ ያሉ ማነቆዎችን ለመቅረፍ የሚያስችሉ ዝርዝር አቅጣጫዎች እንደሚቀመጡበትም ገልጸዋል።
በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ከፍያለው ተፈራ በበኩላቸው፤ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በርካታ የልማት ተግባራት መከናወናቸውንና የማኅበረሰቡም ተሳትፎ ጠንካራ እንደነበር ገልጸዋል።

በዘጠኝ ወራቱ በፈተናዎች ውስጥ አልፎ ትልቅ ውጤት መመዝገቡን የተናገሩት ኃላፊው፤ በቀረው አጭር የበጀት ዓመቱ ወራት ውስጥ ያልተከናወኑ ሥራዎችን በላቀ ቁርጠኝነት በማከናወን የማኅበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መሥራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
የመንግስት የማስፈጸም አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን ባለፉት ዘጠኝ ወራት የተከናወኑ ተግባራት የሚያሳዩ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...
Apr 14, 2026
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026
Jul 17, 2025