🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ መንግስት የግል ባለሃብቶች በኢንደስትሪ ፓርኮች ኢንቨስትመንት እንዲሰማሩ እንደሚያበረታታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
“የሉዓላዊነት ልብ” በሚል ርዕሰ ጉዳይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር ቆይታ አድርገዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከለውጡ ወዲህ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ብዛት እና ቁጥር ላይ ብቻ ሳይወሰኑ ጥራት ላይ እንዲያተኩሩ፣ በቅንጅት እንዲሰሩ መንግስት አመቻች ሆኖ እየሰራ መሆኑን ገልፀው፤ አሁን ካሉት 26 ኢንደስትሪ ፓርኮች ሰባቱ የግል መሆናቸውን ተናግረዋል።
የግል ኢንደስትሪ ፓርክ እየሰፋ መሄድ እንዳለበት አቋም መያዙን ተናግረው ኤ ኤም ጂ ን እና ኦዳን ለአብነት አንስተዋል፡፡
የግል ኢንደስትሪ ፓርኮች ብረትን በማቅለጥ፣ የመኪና መለዋወጫን በመስራትና ከባድ ኢንደስትሪ ላይ ማተኮራቸውን ተናግረው ኢንደስትሪዎቹ በስፋት፣ በቅንጅት፣ በሚያመርቱት ምርትና በውጤታቸውም የተሻሉ ናቸው ብለዋል፡፡
ኢንቨስትመንትን ለመሳብ፣ የመሰረተ ልማት ወጪን በመቀነስ፣ ቅንጅት በመፍጠር አንዱ ለአንዱ ግብአት በመሆንም ተመራጭ መሆናቸውን አብራርተዋል፣ የኢንደስትሪ ፓርክም ለኢምፖርት ኤክስፖርት አመቺነት ባለው ቦታም እንደሚሰሩ ገልፀዋል፡፡
ከለውጡ በፊት የኢንደስትሪ ፓርኮች ህንፃ ግንባታ ላይ ብቻ ይተኮር እንደነበር ገልፀው፤ የውስጥ አቅም ያልገነባ፣ ወጪያቸው ከፍተኛ፣ የአዋጭነት ሁኔታቸው ያልተጠና እና ለብክነት ተጋላጭ ነበሩ ብለዋል፡፡
ከለውጡ ወዲህ የውስጥ አቅምን በመጠቀም የግንባታ ወጪን መቀነስ መቻሉን ስራ ማስጀመር እና ምርታማነት ላይ መተኮሩንም ተናግረዋል ፡፡
በዚህም ምርታማነት ማደጉንና አሁንም መሻሻል እንደሚገባው ተናግረዋል፡፡
ኤክስፖርት ከለውጡ በፊት ከነበረበት 51 ሚሊየን ዶላር በቀጣይ አመት ወደ 1 ቢሊየን ዶላር ያድጋል ተብሎ እንደሚጠበቅም ገልጸዋል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026