🔇Unmute
ባህር ዳር፤ ሚያዚያ 10/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ከ919 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች በተለያዩ መስኮች የስራ እድል መፈጠሩን የክልሉ ስራና ስልጠና ቢሮ ገለጸ።
የቢሮው የስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተር ፕራይዞች ልማት ዳይሬክተር አቶ ስላባት ሰውአገኝ ለኢዜአ እንደገለፁት ዜጎችን የስራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው።
በዚህም በበጀት ዓመቱ አንድ ነጥብ አንድ ሚሊዮን ለሚጠጉ ዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር ግብ ተይዞ በተደረገ ሁሉን አቀፍ ጥረት በዘጠኝ ወሩ ለ919 ሺህ 475 ዜጎች የስራ ዕድል መፍጠር መቻሉን ገልፀዋል።
የስራ ዕድሉ ከተፈጠረባቸው መስኮች መካከልም ከ125 ሺህ 300 በላይ የሚሆኑት በውጭ ሀገር የስራ ስምሪት መሆኑን ገልጸዋል።
የስራ ዕድሉ በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በአገልግሎት ዘርፎች መሆኑን ገልጸው፤ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በድምሩ ለ919 ሺህ 475 ዜጎች የስራ ዕድል ተፈጥሯል ብለዋል።
ዳይሬክተሩ እንዳሉት 1 ሺህ 347 የመስሪያ ሼዶች እንዲሁም ለከተማ ግብርና፣ ለማዕድን ማውጫና ለሌሎች የግብርና ልማት ተግባራት 11 ሺህ 444 ሄክታር መሬት ለኢንተርፕራይዞች መተላለፉንም ተናግረዋል።
የመስሪያ ገንዘብ ለሚያስፈልጋቸው ኢንተርፕራይዞች ከ5 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ የብድር አቅርቦት የተመቻቸ ስለመሆኑም አንስተዋል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026