🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ) ፦ ኢትዮጵያ እና እንግሊዝ በልማት እና በኢንቨስትመንት ያላቸውን ግንኙነት ለማጠናከር ተስማምተዋል።
በዋሺንግተን ዲሲ ሲካሔድ ከቆየው የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የዓለም ባንክ ዓመታዊ የፀደይ ወቅት ስብሰባ ጎን ለጎን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ከእንግሊዙ ዓለም አቀፍ ልማት ሚኒስትር ባሮኒስ ቻፕማን ጋር ተወያይተዋል።
በውይይታቸውም በሁለቱ ሃገራት መካከል ያለውን የልማት የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብርና አጋርነት ለማጠናከር ተስማምተዋል።

አቶ አህመድ ሽዴ በኢትዮጵያ ያለውን ጠንካራ የኢኮኖሚ ሪፎርም ሂደትና የተገኙ ስኬቶችን በተመለከተ ገለጻ አደርገዋል።
ኢትዮጵያ ከእንግሊዝ ጋር ያላትን ጠንካራ አጋርነት ያነሱት ሚኒስትሩ የእንግሊዝ መንግስት የሚያደርገውን ድጋፍ አንዲያጠናክርም ጠይቀዋል።
ባሮኒስ ቻፕማን በበኩላቸው ኢትዮጵያ እያካሔደች ያለውን የለውጥ ስራ በማድነቅ የእንግሊዝ መንግስት የልማት አጋርነቱን ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል።
ሚኒስትሯ አያይዘውም ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት ዙሪያ ያላትን ቁልፍ ሚና አንስተዋል።
ሁለቱ ወገኖች በውይይታቸው የሃገራቱን አጋርነት ከማስፋት ባለፈ በንግድ ፣ በልማትና በኢንቨስትመንት እንዲሁም በኢኮኖሚ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማምተዋል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026