🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ) ፦ ኢትዮጵያ እና እንግሊዝ በልማት እና በኢንቨስትመንት ያላቸውን ግንኙነት ለማጠናከር ተስማምተዋል።
በዋሺንግተን ዲሲ ሲካሔድ ከቆየው የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የዓለም ባንክ ዓመታዊ የፀደይ ወቅት ስብሰባ ጎን ለጎን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ከእንግሊዙ ዓለም አቀፍ ልማት ሚኒስትር ባሮኒስ ቻፕማን ጋር ተወያይተዋል።
በውይይታቸውም በሁለቱ ሃገራት መካከል ያለውን የልማት የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብርና አጋርነት ለማጠናከር ተስማምተዋል።

አቶ አህመድ ሽዴ በኢትዮጵያ ያለውን ጠንካራ የኢኮኖሚ ሪፎርም ሂደትና የተገኙ ስኬቶችን በተመለከተ ገለጻ አደርገዋል።
ኢትዮጵያ ከእንግሊዝ ጋር ያላትን ጠንካራ አጋርነት ያነሱት ሚኒስትሩ የእንግሊዝ መንግስት የሚያደርገውን ድጋፍ አንዲያጠናክርም ጠይቀዋል።
ባሮኒስ ቻፕማን በበኩላቸው ኢትዮጵያ እያካሔደች ያለውን የለውጥ ስራ በማድነቅ የእንግሊዝ መንግስት የልማት አጋርነቱን ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል።
ሚኒስትሯ አያይዘውም ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት ዙሪያ ያላትን ቁልፍ ሚና አንስተዋል።
ሁለቱ ወገኖች በውይይታቸው የሃገራቱን አጋርነት ከማስፋት ባለፈ በንግድ ፣ በልማትና በኢንቨስትመንት እንዲሁም በኢኮኖሚ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማምተዋል።
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...
Apr 14, 2026
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026