🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፦ በመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ለሚታዩ መሠረታዊ ችግሮች መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት ወሳኝ መፍትሔ የሚሰጥ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎትን አስጀምረዋል።
የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዚሁ ወቅት፤ ከዓመታት በፊት የመንግሥት አገልግሎቶች ዜጎችን ለብልሹ አሰራርና እንግልት በመዳረግ የዘመናት ጥያቄ ሆነው መቆየታቸውን አስታውሰዋል።
ይህም የዜጎችን ምሬት በማባባስ የኢትዮጵያን ዕድገት የሚጎትት እንደነበር አስገንዝበዋል።
በዚህም ለአገልግሎት የጥራት ችግር መፍትሔ ለማበጀት በመንግስት ደረጃ ተከታታይ ምክክር በማድረግ የዲጂታላይዜሽን ምኅዳር መፍጠር እንደተቻለ አንስተዋል።
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም የመንግሥትን አገልግሎት ከደላላና ከሰው ንክኪ ነፃ የአሰራር ሥርዓት ለዜጎች በማቅረብ አገልግሎትን የሚያሳልጥ ምኅዳር መፍጠሩን ገልጸዋል።
ይህም የሥራ ቅልጥፍን በማሳለጥ ከፍተኛ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል።
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ትላልቅ የመንግሥት አገልግሎቶችን ወደ ዜጎች በማቅረብ የተገልጋዮችን ፍላጎት የሚያሳልጥ ወሳኝ እርምጃ መሆኑን አንስተዋል።
ዜጎች የመንግሥትን አገልግሎት በነፃነት የማግኘት መብት አላቸው ያሉት ሚኒስትሩ፤ በዚህም ዜጎች መንግሥት የዘረጋቸውን ዘመናዊ የአሰራር ስርዓቶች በመጠቀም ግብርን በግልፀኝነት መክፈል እንደሚጠበቅም አስገንዝበዋል።
በአጠቃላይ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ይስተዋል የነበረውን መሠረታዊ ችግር መፍትሄ የሚሰጥ ወሳኝ አሰራር መሆኑን አስረድተዋል።
ዜጎችም የመንግሥትን ዘመናዊ፣ ግልፅና ቀልጣፋ የአሰራር ሥርዓት ሊጠቀምበት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...
Apr 14, 2026
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026