🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፦ በመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ለሚታዩ መሠረታዊ ችግሮች መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት ወሳኝ መፍትሔ የሚሰጥ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎትን አስጀምረዋል።
የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዚሁ ወቅት፤ ከዓመታት በፊት የመንግሥት አገልግሎቶች ዜጎችን ለብልሹ አሰራርና እንግልት በመዳረግ የዘመናት ጥያቄ ሆነው መቆየታቸውን አስታውሰዋል።
ይህም የዜጎችን ምሬት በማባባስ የኢትዮጵያን ዕድገት የሚጎትት እንደነበር አስገንዝበዋል።
በዚህም ለአገልግሎት የጥራት ችግር መፍትሔ ለማበጀት በመንግስት ደረጃ ተከታታይ ምክክር በማድረግ የዲጂታላይዜሽን ምኅዳር መፍጠር እንደተቻለ አንስተዋል።
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም የመንግሥትን አገልግሎት ከደላላና ከሰው ንክኪ ነፃ የአሰራር ሥርዓት ለዜጎች በማቅረብ አገልግሎትን የሚያሳልጥ ምኅዳር መፍጠሩን ገልጸዋል።
ይህም የሥራ ቅልጥፍን በማሳለጥ ከፍተኛ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል።
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ትላልቅ የመንግሥት አገልግሎቶችን ወደ ዜጎች በማቅረብ የተገልጋዮችን ፍላጎት የሚያሳልጥ ወሳኝ እርምጃ መሆኑን አንስተዋል።
ዜጎች የመንግሥትን አገልግሎት በነፃነት የማግኘት መብት አላቸው ያሉት ሚኒስትሩ፤ በዚህም ዜጎች መንግሥት የዘረጋቸውን ዘመናዊ የአሰራር ስርዓቶች በመጠቀም ግብርን በግልፀኝነት መክፈል እንደሚጠበቅም አስገንዝበዋል።
በአጠቃላይ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ይስተዋል የነበረውን መሠረታዊ ችግር መፍትሄ የሚሰጥ ወሳኝ አሰራር መሆኑን አስረድተዋል።
ዜጎችም የመንግሥትን ዘመናዊ፣ ግልፅና ቀልጣፋ የአሰራር ሥርዓት ሊጠቀምበት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026