የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ለሚታዩ ችግሮች ወሳኝ መፍትሔ ነው

Apr 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፦ በመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ለሚታዩ መሠረታዊ ችግሮች መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት ወሳኝ መፍትሔ የሚሰጥ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎትን አስጀምረዋል።

የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዚሁ ወቅት፤ ከዓመታት በፊት የመንግሥት አገልግሎቶች ዜጎችን ለብልሹ አሰራርና እንግልት በመዳረግ የዘመናት ጥያቄ ሆነው መቆየታቸውን አስታውሰዋል።

ይህም የዜጎችን ምሬት በማባባስ የኢትዮጵያን ዕድገት የሚጎትት እንደነበር አስገንዝበዋል።

በዚህም ለአገልግሎት የጥራት ችግር መፍትሔ ለማበጀት በመንግስት ደረጃ ተከታታይ ምክክር በማድረግ የዲጂታላይዜሽን ምኅዳር መፍጠር እንደተቻለ አንስተዋል።

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም የመንግሥትን አገልግሎት ከደላላና ከሰው ንክኪ ነፃ የአሰራር ሥርዓት ለዜጎች በማቅረብ አገልግሎትን የሚያሳልጥ ምኅዳር መፍጠሩን ገልጸዋል።

ይህም የሥራ ቅልጥፍን በማሳለጥ ከፍተኛ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል።

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ትላልቅ የመንግሥት አገልግሎቶችን ወደ ዜጎች በማቅረብ የተገልጋዮችን ፍላጎት የሚያሳልጥ ወሳኝ እርምጃ መሆኑን አንስተዋል።

ዜጎች የመንግሥትን አገልግሎት በነፃነት የማግኘት መብት አላቸው ያሉት ሚኒስትሩ፤ በዚህም ዜጎች መንግሥት የዘረጋቸውን ዘመናዊ የአሰራር ስርዓቶች በመጠቀም ግብርን በግልፀኝነት መክፈል እንደሚጠበቅም አስገንዝበዋል።

በአጠቃላይ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ይስተዋል የነበረውን መሠረታዊ ችግር መፍትሄ የሚሰጥ ወሳኝ አሰራር መሆኑን አስረድተዋል።

ዜጎችም የመንግሥትን ዘመናዊ፣ ግልፅና ቀልጣፋ የአሰራር ሥርዓት ሊጠቀምበት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026