የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ለህብረተሰቡ የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመስጠት ተዘጋጅተናል

Apr 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ ለህብረተሰቡ የተለያዩ መንግሥታዊ አገልግሎቶችን በተቀላጠፈ መንገድ ለመስጠት ተዘጋጅተናል ሲሉ የመሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት ሰራተኞች ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአይነቱ ልዩና የመጀመሪያ የሆነውን መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት አስጀምረዋል።

በአገልግሎቱ የስምንት ተቋማትን አገልግሎቶች በአንድ ላይ በማቀናጀት በይፋ ስራ የጀመረ ሲሆን፤ ይህም ለህዝብ የሚሰጡ ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን ይበልጥ ተደራሽ እና ቀልጣፋ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።


በዚህ ተንቀሳቃሽ የአውቶቡስ አገልግሎት የተጀመሩ አገልግሎቶችም፣ የገቢ (አዲስ ቲን ማውጣት)፣ የንግድ (ንግድ ፈቃድ ማውጣት፣ ማደስ)፣ የጤና (ለመንጃ ፈቃድ አካላዊ የጤና ምርመራ)፣ የሲቪል ምዝገባ (የመታወቂያ ዕድሳት እና ልደት)፣ የአሸከረካሪ ተሽከርካሪ (የመንጃ ፈቃድ እና የቦሎ ዕድሳት)፣ የኢትዮ ፖስታ (የመንገድ ፈንድ ክፍያ)፣ የብሔራዊ መታወቂያ (አዲስ ምዝገባና የመረጃ እርማት) እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት (ቅድመ ክፍያ) ናቸው።

በመሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት እንዲሰጡ የተመደቡ የልዩ ልዩ ተቋማት ሰራተኞች፣ መንግሥታዊ አገልግሎቶችን በዘመናዊና ቀልጣፋ መንገድ ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ መዘጋጀታቸውን አረጋግጠዋል።

በሲቪል ምዝገባና ነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የአዲስ መሶብ አገልግሎት አስተባባሪ ዳኜ መኮንን ኤጀንሲው በተንቀሳቃሽ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ላይ ለህብረተሰቡ ከሲቪል ምዝገባና ነዋሪነት አገልግሎት ጋር የተገናኙ አስር ልዩ ልዩ አገልግሎቶችን ለመስጠት ወደ ስራ ገብተናል ብለዋል።


ለአገልግሎት ፈላጊ ደንበኞች ከሚሰጧቸው አገልግሎቶች መካከል የዲጂታል መታወቂያ እድሳት፣ የልደት ካርድ ማውጣት፣ የጉዲፈቻና ያላገባ ሰርተፊኬት መስጠት ተጠቃሽ መሆናቸውን አብራርተዋል።

የመሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት ውስጥ የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን የደንበኞች አገልግሎት ባለሙያ አስናቀ ወርቁ በበኩላቸው፣ ባለስልጣኑ በማዕከሉ የመንጃ ፈቃድ እድሳትን፣ የዓመታዊ የብቃት ማረጋገጫ ቦሎና የተበላሸ ቦሎ ግልባጭ እንዲሁም የጠፋ ቦሎ ምትክ የመስጠት አገልግሎቶችን ለደንበኞች እንደሚያቀርብ ገልጸዋል።


በመሶብ ተንቀሳቃሽ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የጤና ምርመራ ዘርፍ የሚያገለግሉት አቶ ጉቱ ከበደ በበኩላቸው፤ በተለይም ለመንጃ ፈቃድ ዕድሳት የሚመጡ ደንበኞችን ጨምሮ ለተለያዩ አገልግሎቶች አስፈላጊ የጤና ምርመራዎችን በማድረግ ላይ እንገኛለን ብለዋል።


በገቢዎች ቢሮ የደንበኞች አገልግሎት ባለሙያ ጫልቱ ታደሰ፣ ቢሮው ከሚሰጣቸው ልዩ ልዩ አገልግሎቶች መካከል በዋናነት የሚጠቀሰውን የንግድ መለያ ቁጥር (ቲን ነምበር) የመስጠት ተግባር በተንቀሳቃሽ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አማካኝነት ለነዋሪዎች እንደሚያቀርቡ ገልጸዋል።


የኢትዮጵያ ፖስታ ባለሙያ ሙላቷ አበዙ ድርጅታቸው በመሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት ውስጥ የመንገድ ፈንድ አገልግሎት እና የፋይዳ መታወቂያ ህትመት የሚፈልጉ ደንበኞችን ለማስተናገድ መዘጋጀቷን ተናግራለች።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የማዕድን ሀብት ልማት ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ አቅም እየሆነ ነው

ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...

Jun 10, 2026

የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ የሕዝብን ሀብት ለልማት በማዋል በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...

Jun 9, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...

May 28, 2026

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026