🔇Unmute
ነጌሌ ቦረና፤ ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- በምሥራቅ ቦረና ዞን ለ450 ሺህ የቤት እንስሳት የክትባት አገልግሎት በዘመቻ መልክ እየተሰጠ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለጸ፡፡
በጽሕፈት ቤቱ የእንስሳት ጤና ባለሙያ በነያ አሬሮ ለኢዜአ እንዳሉት፤ እየጣለ ያለውን የበልግ ዝናብ ተከትሎ ሊቀሰቀስ የሚችለውን የእንስሳት በሽታ አስቀድሞ ለመከላከል የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው።

440 የእንስሳት ሐኪሞችና በርካታ ድጋፍ ሰጭ ሠራተኞች ለእንስሳቱ ክትባት እየሰጡ መሆኑንም ገልጸዋል።
በዞኑ ስምንት ቆላማ ወረዳዎች በሚካሄው የእንስሳት ክትባት ዘመቻ፤ 450 ሺህ የቤት እንስሳትን ተደራሽ ለማድረግ ታቅዷል ብለዋል።
እስካሁንም ለ60 ሺህ 849 የቤት እንስሳት የክትባት አገልግሎት መሰጠቱን ጠቅሰው፤ የክትባት አገልግሎቱ በዋናነት እየተሰጠ ያለው ለግመሎች፣ ለዳልጋና ለጋማ ከብቶች እንዲሁም ለበግና ፍየሎች መሆኑን አብራርተዋል።

ክትባቱን ሙሉ በሙሉ ተደራሽ ለማድረግ 450 ሺህ ዶዝ የክትባት መድኃኒት መቅረቡን ተናግረዋል።
በተለይም ክትባቱ የሳንባ ምች፣ አባ ሰንጋ፣ አባ ጎርባና ሌሎችንም የእንስስት በሽታዎች አስቀድሞ ለመከላከል እንደሚያስችልም አስገንዝበዋል።
የክትባት አገልግሎቱ ተደራሽ መሆን፤ አርብቶ አደሩ እና ከፊል አርብቶ አደሩ ከእንስሳት ተዋፅዖ የሚያገኘውን ጥቅም ለማሳደግና የምግብ ዋስትናቸውን በዘላቂነት ለማረጋገጥ የጎላ ፋይዳ አለው ብለዋል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026