🔇Unmute
ነጌሌ ቦረና፤ ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- በምሥራቅ ቦረና ዞን ለ450 ሺህ የቤት እንስሳት የክትባት አገልግሎት በዘመቻ መልክ እየተሰጠ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለጸ፡፡
በጽሕፈት ቤቱ የእንስሳት ጤና ባለሙያ በነያ አሬሮ ለኢዜአ እንዳሉት፤ እየጣለ ያለውን የበልግ ዝናብ ተከትሎ ሊቀሰቀስ የሚችለውን የእንስሳት በሽታ አስቀድሞ ለመከላከል የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው።

440 የእንስሳት ሐኪሞችና በርካታ ድጋፍ ሰጭ ሠራተኞች ለእንስሳቱ ክትባት እየሰጡ መሆኑንም ገልጸዋል።
በዞኑ ስምንት ቆላማ ወረዳዎች በሚካሄው የእንስሳት ክትባት ዘመቻ፤ 450 ሺህ የቤት እንስሳትን ተደራሽ ለማድረግ ታቅዷል ብለዋል።
እስካሁንም ለ60 ሺህ 849 የቤት እንስሳት የክትባት አገልግሎት መሰጠቱን ጠቅሰው፤ የክትባት አገልግሎቱ በዋናነት እየተሰጠ ያለው ለግመሎች፣ ለዳልጋና ለጋማ ከብቶች እንዲሁም ለበግና ፍየሎች መሆኑን አብራርተዋል።

ክትባቱን ሙሉ በሙሉ ተደራሽ ለማድረግ 450 ሺህ ዶዝ የክትባት መድኃኒት መቅረቡን ተናግረዋል።
በተለይም ክትባቱ የሳንባ ምች፣ አባ ሰንጋ፣ አባ ጎርባና ሌሎችንም የእንስስት በሽታዎች አስቀድሞ ለመከላከል እንደሚያስችልም አስገንዝበዋል።
የክትባት አገልግሎቱ ተደራሽ መሆን፤ አርብቶ አደሩ እና ከፊል አርብቶ አደሩ ከእንስሳት ተዋፅዖ የሚያገኘውን ጥቅም ለማሳደግና የምግብ ዋስትናቸውን በዘላቂነት ለማረጋገጥ የጎላ ፋይዳ አለው ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...
Apr 14, 2026
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026