የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በምሥራቅ ቦረና ዞን ለቤት እንስሳት ክትባት እየተሰጠ ነው

Apr 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ነጌሌ ቦረና፤ ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- በምሥራቅ ቦረና ዞን ለ450 ሺህ የቤት እንስሳት የክትባት አገልግሎት በዘመቻ መልክ እየተሰጠ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለጸ፡፡

በጽሕፈት ቤቱ የእንስሳት ጤና ባለሙያ በነያ አሬሮ ለኢዜአ እንዳሉት፤ እየጣለ ያለውን የበልግ ዝናብ ተከትሎ ሊቀሰቀስ የሚችለውን የእንስሳት በሽታ አስቀድሞ ለመከላከል የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው።


440 የእንስሳት ሐኪሞችና በርካታ ድጋፍ ሰጭ ሠራተኞች ለእንስሳቱ ክትባት እየሰጡ መሆኑንም ገልጸዋል።

በዞኑ ስምንት ቆላማ ወረዳዎች በሚካሄው የእንስሳት ክትባት ዘመቻ፤ 450 ሺህ የቤት እንስሳትን ተደራሽ ለማድረግ ታቅዷል ብለዋል።

እስካሁንም ለ60 ሺህ 849 የቤት እንስሳት የክትባት አገልግሎት መሰጠቱን ጠቅሰው፤ የክትባት አገልግሎቱ በዋናነት እየተሰጠ ያለው ለግመሎች፣ ለዳልጋና ለጋማ ከብቶች እንዲሁም ለበግና ፍየሎች መሆኑን አብራርተዋል።


ክትባቱን ሙሉ በሙሉ ተደራሽ ለማድረግ 450 ሺህ ዶዝ የክትባት መድኃኒት መቅረቡን ተናግረዋል።

በተለይም ክትባቱ የሳንባ ምች፣ አባ ሰንጋ፣ አባ ጎርባና ሌሎችንም የእንስስት በሽታዎች አስቀድሞ ለመከላከል እንደሚያስችልም አስገንዝበዋል።

የክትባት አገልግሎቱ ተደራሽ መሆን፤ አርብቶ አደሩ እና ከፊል አርብቶ አደሩ ከእንስሳት ተዋፅዖ የሚያገኘውን ጥቅም ለማሳደግና የምግብ ዋስትናቸውን በዘላቂነት ለማረጋገጥ የጎላ ፋይዳ አለው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026