የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በምሥራቅ ቦረና ዞን ለቤት እንስሳት ክትባት እየተሰጠ ነው

Apr 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ነጌሌ ቦረና፤ ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- በምሥራቅ ቦረና ዞን ለ450 ሺህ የቤት እንስሳት የክትባት አገልግሎት በዘመቻ መልክ እየተሰጠ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለጸ፡፡

በጽሕፈት ቤቱ የእንስሳት ጤና ባለሙያ በነያ አሬሮ ለኢዜአ እንዳሉት፤ እየጣለ ያለውን የበልግ ዝናብ ተከትሎ ሊቀሰቀስ የሚችለውን የእንስሳት በሽታ አስቀድሞ ለመከላከል የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው።


440 የእንስሳት ሐኪሞችና በርካታ ድጋፍ ሰጭ ሠራተኞች ለእንስሳቱ ክትባት እየሰጡ መሆኑንም ገልጸዋል።

በዞኑ ስምንት ቆላማ ወረዳዎች በሚካሄው የእንስሳት ክትባት ዘመቻ፤ 450 ሺህ የቤት እንስሳትን ተደራሽ ለማድረግ ታቅዷል ብለዋል።

እስካሁንም ለ60 ሺህ 849 የቤት እንስሳት የክትባት አገልግሎት መሰጠቱን ጠቅሰው፤ የክትባት አገልግሎቱ በዋናነት እየተሰጠ ያለው ለግመሎች፣ ለዳልጋና ለጋማ ከብቶች እንዲሁም ለበግና ፍየሎች መሆኑን አብራርተዋል።


ክትባቱን ሙሉ በሙሉ ተደራሽ ለማድረግ 450 ሺህ ዶዝ የክትባት መድኃኒት መቅረቡን ተናግረዋል።

በተለይም ክትባቱ የሳንባ ምች፣ አባ ሰንጋ፣ አባ ጎርባና ሌሎችንም የእንስስት በሽታዎች አስቀድሞ ለመከላከል እንደሚያስችልም አስገንዝበዋል።

የክትባት አገልግሎቱ ተደራሽ መሆን፤ አርብቶ አደሩ እና ከፊል አርብቶ አደሩ ከእንስሳት ተዋፅዖ የሚያገኘውን ጥቅም ለማሳደግና የምግብ ዋስትናቸውን በዘላቂነት ለማረጋገጥ የጎላ ፋይዳ አለው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026