🔇Unmute
ድሬዳዋ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- በድሬዳዋ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ 84 የተዘጉና በግንባታ ላይ የነበሩ አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት መሸጋገራቸውን የአስተዳደሩ ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ገለፀ።
በአስተዳደሩ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በአምራች ኢንዱስትሪዎች ዘርፍ እየተመዘገቡ የሚገኙ ውጤቶችን የሚያሳይ "ድሬ ታምርት፤ ኢትዮጵያ ትበልፅግ" በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀ የኢንዱስትሪ ኤክስፖ ነገ ይጀመራል።
ኤክስፖውን አስመልክተው የአስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ኡስማን አህመድ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል።
አቶ ኡስማን እንደገለጹት፤ ባለፉት አራት ዓመታት በተካሄደው እና ዘንድሮም በቀጠለው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ተዘግተውና በግንባታ ላይ የነበሩ 84 አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት ተሸጋግረዋል።
በንቅናቄው በተደረጉ ልዩ ድጋፍ እና ክትትሎች የመካከለኛ እና ከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች የፋይናንስ፣ የመሬት፣ የመሠረተ ልማት፣ የኤሌክትሪክ እና የሌሎች አገልግሎት ጥያቄዎች በተቀናጀ መልኩ መፈታታቸውን አንስተዋል።
ከ34 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡት እነዚሁ ኢንዱስትሪዎች 87 ዓይነት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በራስ አቅም በማምረት የውጭ ምንዛሬን እያስቀሩ ይገኛሉ ብለዋል።
ከ17 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ ዕድል መፍጠራቸውንም አንስተዋል።
ለአራተኛ ጊዜ የተዘጋጀው እና ነገ በይፋ በሚጀመረው ኤክስፖው ላይ 50 አምራች ኢንዱስትሪዎች የተለያዩ ምርቶቻቸውን በማስተዋወቅ የገበያ፣ የግብአትና የእርስ በርስ መመጋገብ እና ትስስር እንደሚፈጥሩ ተናግረዋል።
ለአንድ ሳምንት በሚዘልቀው ኤክስፖው ላይ የፌደራልና የድሬዳዋ አስተዳደር ከፍተኛ የዘርፉ አመራሮች እንደሚሳተፉም ይጠበቃል።
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...
Apr 14, 2026
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026