የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በድሬዳዋ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ 84 የተዘጉና በግንባታ ላይ የነበሩ ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት ተሸጋግረዋል

Apr 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ድሬዳዋ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- በድሬዳዋ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ 84 የተዘጉና በግንባታ ላይ የነበሩ አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት መሸጋገራቸውን የአስተዳደሩ ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ገለፀ።

በአስተዳደሩ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በአምራች ኢንዱስትሪዎች ዘርፍ እየተመዘገቡ የሚገኙ ውጤቶችን የሚያሳይ "ድሬ ታምርት፤ ኢትዮጵያ ትበልፅግ" በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀ የኢንዱስትሪ ኤክስፖ ነገ ይጀመራል።

ኤክስፖውን አስመልክተው የአስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ኡስማን አህመድ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል።

አቶ ኡስማን እንደገለጹት፤ ባለፉት አራት ዓመታት በተካሄደው እና ዘንድሮም በቀጠለው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ተዘግተውና በግንባታ ላይ የነበሩ 84 አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት ተሸጋግረዋል።

በንቅናቄው በተደረጉ ልዩ ድጋፍ እና ክትትሎች የመካከለኛ እና ከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች የፋይናንስ፣ የመሬት፣ የመሠረተ ልማት፣ የኤሌክትሪክ እና የሌሎች አገልግሎት ጥያቄዎች በተቀናጀ መልኩ መፈታታቸውን አንስተዋል።

ከ34 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡት እነዚሁ ኢንዱስትሪዎች 87 ዓይነት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በራስ አቅም በማምረት የውጭ ምንዛሬን እያስቀሩ ይገኛሉ ብለዋል።

ከ17 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ ዕድል መፍጠራቸውንም አንስተዋል።

ለአራተኛ ጊዜ የተዘጋጀው እና ነገ በይፋ በሚጀመረው ኤክስፖው ላይ 50 አምራች ኢንዱስትሪዎች የተለያዩ ምርቶቻቸውን በማስተዋወቅ የገበያ፣ የግብአትና የእርስ በርስ መመጋገብ እና ትስስር እንደሚፈጥሩ ተናግረዋል።

ለአንድ ሳምንት በሚዘልቀው ኤክስፖው ላይ የፌደራልና የድሬዳዋ አስተዳደር ከፍተኛ የዘርፉ አመራሮች እንደሚሳተፉም ይጠበቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026