🔇Unmute
ድሬዳዋ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- በድሬዳዋ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ 84 የተዘጉና በግንባታ ላይ የነበሩ አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት መሸጋገራቸውን የአስተዳደሩ ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ገለፀ።
በአስተዳደሩ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በአምራች ኢንዱስትሪዎች ዘርፍ እየተመዘገቡ የሚገኙ ውጤቶችን የሚያሳይ "ድሬ ታምርት፤ ኢትዮጵያ ትበልፅግ" በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀ የኢንዱስትሪ ኤክስፖ ነገ ይጀመራል።
ኤክስፖውን አስመልክተው የአስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ኡስማን አህመድ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል።
አቶ ኡስማን እንደገለጹት፤ ባለፉት አራት ዓመታት በተካሄደው እና ዘንድሮም በቀጠለው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ተዘግተውና በግንባታ ላይ የነበሩ 84 አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት ተሸጋግረዋል።
በንቅናቄው በተደረጉ ልዩ ድጋፍ እና ክትትሎች የመካከለኛ እና ከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች የፋይናንስ፣ የመሬት፣ የመሠረተ ልማት፣ የኤሌክትሪክ እና የሌሎች አገልግሎት ጥያቄዎች በተቀናጀ መልኩ መፈታታቸውን አንስተዋል።
ከ34 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡት እነዚሁ ኢንዱስትሪዎች 87 ዓይነት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በራስ አቅም በማምረት የውጭ ምንዛሬን እያስቀሩ ይገኛሉ ብለዋል።
ከ17 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ ዕድል መፍጠራቸውንም አንስተዋል።
ለአራተኛ ጊዜ የተዘጋጀው እና ነገ በይፋ በሚጀመረው ኤክስፖው ላይ 50 አምራች ኢንዱስትሪዎች የተለያዩ ምርቶቻቸውን በማስተዋወቅ የገበያ፣ የግብአትና የእርስ በርስ መመጋገብ እና ትስስር እንደሚፈጥሩ ተናግረዋል።
ለአንድ ሳምንት በሚዘልቀው ኤክስፖው ላይ የፌደራልና የድሬዳዋ አስተዳደር ከፍተኛ የዘርፉ አመራሮች እንደሚሳተፉም ይጠበቃል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026