የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ባለፉት ዘጠኝ ወራት 4 ነጥብ 85 ቢሊየን ዶላር የሚያወጡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ መተካት ተችሏል

Apr 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ 4 ነጥብ 85 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጡ ገቢ ምርቶችን በሀገር ውስጥ መተካት መቻሉን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ።

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለዘርፉ ትልቅ መሰረት መጣሉን የገለጹት ሚኒስትሩ፣ በገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽን 754 ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት መግባታቸውን ጠቁመዋል።

የ2018 በጀት ዓመት ሦስተኛው የመቶ ቀናት እና የዘጠኝ ወራት ስራ አፈጻጸም ሪፖርት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተገምግሟል።

የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በሰጡት ማብራሪያ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግርን በማሳካት ረገድ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን አንስተዋል።

የሪፎርም ሥራዎቹ ምርትና ምርታማነትን በመጨመር እንዲሁም የዜጎችን ኑሮ በማሻሻል ስኬታማ መሆናቸውን አንስተዋል።

ቀደም ሲል 4 ነጥብ 8 በመቶ ብቻ የነበረው የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ዕድገት አሁን ላይ በሁለት አሃዝ አድጎ ከ13 በመቶ በላይ ደርሷል ነው ያሉት።

የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሀብቶች ገቢ ምርትን በመተካትና በወጪ ንግድ ዘርፍ አመርቂ ለውጥ ማምጣታቸውን ጠቁመዋል።

ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ 433 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ የኢንዱስትሪ ምርቶች ለውጭ ገበያ የቀረቡ ሲሆን የዘርፉ የኃይል አጠቃቀምም ማደጉን ተናግረዋል።

የገቢ ምርትን በሀገር ውስጥ ለመተካት በተሠራው ሥራ 4 ነጥብ 85 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጡ ተኪ ምርቶችን ማምረት መቻሉን አስታውቀዋል።

ይህ ውጤት የኑሮ ጫናን በማቅለል እና የኢኮኖሚ መነቃቃትን በማምጣት ረገድ ትልቅ ሚና መጫወቱን አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለዘርፉ ትልቅ መሰረት መጣሉን የገለጹት ሚኒስትሩ፣ በገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽን 754 ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት መግባታቸውን ጠቁመዋል።

በቀጣይም የምርት አቅምን ለማሳደግ የፋይናንስ፣ የግብዓት፣ የኃይል አቅርቦት እና ምቹ የገበያ ሁኔታዎችን በመፍጠር ላይ በትኩረት እንደሚሰራ አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026