የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልትና አላስፈላጊ ወጪን አስቀርቶልናል - ተገልጋዮች

Apr 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሆሳዕና፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልት እና ያልተገባ ወጪን እንዳስቀረላቸው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሆሳዕና ከተማ ተገልጋዮች ገለፁ፡፡

በማዕከሉ አገልግሎት በማግኘት ላይ የነበሩት አቶ ዮናስ ሴራሞ ለኢዜአ እንደገለፁት ፤የገቢ ግብር ጉዳይ ላይ አገልግሎት ለማግኘት ወደ ማዕከሉ እንደመጡና ባጠረ ጊዜም የሚፈልጉትን ፈጽመው ለመመለስ መቻላቸውን ነው የሚገልጹት።


የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ተገልጋይን ከአላስፈላጊ ከሆነ እንግልትና ወጪ እንደሚታደግ በተግባር ያረጋገጡ መሆኑንም ተናግረዋል።

የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ለማውጣት ወደ ማዕከሉ የመጣው ወጣት ሞላልኝ ታምራት በወቅቱ አገልግሎቱን ማግኘቱን እናማዕከሉ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ይታይ የነበረውን የመልካም አስተዳደር ችግር በመቅረፍ ለማሕበረሰቡ አስፈላጊ የሆነ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ነው የገለጸው።



በማዕከሉ የተገልጋዩን ክብር የጠበቀ እና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኝቷ እንዳስደሰታት የምትገልፀው ደግሞ ወጣት በረከት ዱቲሶ ናት፡፡


በፋይዳ መታወቂያዋ ላይ ያጋጠማትን የስም ስህተት በአጭር ጊዜ ማስተካከል ችያለሁ ብላለች።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ከበደ ሻሜቦ ማዕከሉ በስምንት ተቋማት 27 አገልግሎቶችን እየሰጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡


እስካሁን ድረስ ከ 20 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች አገልግሎት መስጠት መቻሉንም አስረድተዋል፡፡

በከተሞች በመሬት ዘርፍ የሚሰጡና ለብልሹ አሰራር ተጋላጭ የሆኑ አዳዲስ 48 አገልግሎቶች ተለይተዉ በማዕከሉ ውስጥ አገልግሎት ለመስጠት እንዲቻልም ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝም ገልፀዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026