የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የማህበራቱን አደረጃጀት በማዘመን የአርሶና አርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመረው የሪፎርም ስራ ይጠናከራል

Apr 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ የህብረት ስራ ማህበራትን አደረጃጀት በማዘመን የአርሶና አርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመረው የሪፎርም ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ተናገሩ።

የኢትዮጵያ ህብረት ሥራ ኮሚሽን “ወደ ቀበሌ መድረስ” በሚል መሪ ሃሳብ በተለያዩ ስድስት ከተሞች ሲያካሂድ የቆየውን 2ኛውን ሀገር አቀፍ የህብረት ሥራ ማህበራት ሪፎርም የንቅናቄ መድረክ ዛሬ አጠናቋል።

በሀዋሳ በተካሔደው የማጠናቀቂያ መርሃ ግብር ላይ የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ በቪዲዮ ኮንፈረንስ ባስተላለፉት መልዕክት እንዳሉት፤ ባለፉት ስምንት ዓመታት በተለያዩ መስኮች የበለጸገችና ህብረ ብሔራዊት ሀገር ለመፍጠር ዘርፈ ብዙ የሪፎርም ስራዎች ተግባራዊ ተደርገዋል።

በተከናወኑ ተግባራትም ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆኑን አክለዋል።

የመንግስትን፣ የግሉ ዘርፍንና የዜጎችን የካፒታል አቅምና ዕውቀትን ደምሮ የሚይዙት የህብረት ስራ ማህበራት መሆናቸውን በግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲው በግልጽ መቀመጡን ጠቁመዋል።

ማህበራቱ ግብርናውን በማሻገር የአርሶና አርብቶ አደሩን ህይወት መቀየር ረገድ ትልቅ አቅም እንዳላቸው ገልፀው የፋይናንስ አቅርቦት ችግርን በመፍታትና የግብይት ሰንሰለቱን በማሳጠር የሸማቹን ህብረተሰብ ሸክም እንደሚያቀሉም አስረድተዋል።

በንቅናቄ መድረኩ የተሳተፉት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ህብረት ስራ ኤጀንሲ የህብረት ስራ ማህበራት ማደራጃና ማስፋፊያ ዳይሬክተር አቶ ቶንጃ ቶማ በበኩላቸው፤ ማህበራቱ ገበያን በማረጋጋት፣ የአርሶ አደሩን ምርታማነት የሚያሳድጉ ግብዓት በማቅረብና በሌሎች ዘርፎች አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው ብለዋል።


በተለይ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የማህበራቱን አቅም ለማሳደግ በተደረገ የሪፎርም ስራ በኢኮኖሚው ውስጥ ያላቸው አበርክቶ እንዲያድግ ማድረጉን ተናግረዋል።

የኦሮሚያ ክልል ህብረት ስራ ልማት ኤጀንሲ ተወካይ ወይዘሮ ሹሬ እጅቢቾ፤ በክልሉ የህብረት ስራ ማህበራትን አሰራር፣ አደረጃጀትና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ በማተኮር ሪፎርም መሰራቱን ገልጸዋል፡፡


በዚህም ጠንካራ ማህበራት እንዲኖሩ አንድ ላይ የማደራጀት ስራ መሰራቱን ጠቅሰው በንቅናቄ መድረኩ የተገኘውን ልምድና እውቀት ተግባራዊ በማድረግ ለማህበራት ውጤታማነት እንደሚሰሩም ተናግረዋል፡፡

የሲዳማ ክልል ህብረት ስራ ኤጀንሲ የህብረት ስራ ማህበራት ማደራጃና ማስፋፊያ ዳይሬክተር አቶ ደምበሎ ዶንጊሶ በበኩላቸው፤ በሪፎርሙ የማህበራቱን ትርፋማነት፣ የአባላት ተጠቃሚነት ከማጎልበት አንጻር ለውጥ ማምጣት ተችሏል ብለዋል።


ከዚህም ባለፈ በአሰራር ስርዓት በአመራርና በአደረጃጀት የጠነከሩና የፋይናንስ አያያዛቸውን ያዘመኑ ማህበራት መፍጠር እንደተቻለ ገልጸው የተገኘውን ውጤት አጠናክሮ ለማስቀጠል የንቅናቄ መድረኩ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ነው የገለጹት።

ላለፉት ስምንት ቀናት በሀዋሳ ሲካሄድ በቆየው መድረክ ላይ ከሲዳማ፣ ከደቡብ ኢትዮጵያና ከኦሮሚያ ክልል የተውጣጡ 900 የቀበሌ ህብረት ስራ ማህበራት አደረጃጀት ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026