የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የማህበራቱን አደረጃጀት በማዘመን የአርሶና አርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመረው የሪፎርም ስራ ይጠናከራል

Apr 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ የህብረት ስራ ማህበራትን አደረጃጀት በማዘመን የአርሶና አርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመረው የሪፎርም ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ተናገሩ።

የኢትዮጵያ ህብረት ሥራ ኮሚሽን “ወደ ቀበሌ መድረስ” በሚል መሪ ሃሳብ በተለያዩ ስድስት ከተሞች ሲያካሂድ የቆየውን 2ኛውን ሀገር አቀፍ የህብረት ሥራ ማህበራት ሪፎርም የንቅናቄ መድረክ ዛሬ አጠናቋል።

በሀዋሳ በተካሔደው የማጠናቀቂያ መርሃ ግብር ላይ የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ በቪዲዮ ኮንፈረንስ ባስተላለፉት መልዕክት እንዳሉት፤ ባለፉት ስምንት ዓመታት በተለያዩ መስኮች የበለጸገችና ህብረ ብሔራዊት ሀገር ለመፍጠር ዘርፈ ብዙ የሪፎርም ስራዎች ተግባራዊ ተደርገዋል።

በተከናወኑ ተግባራትም ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆኑን አክለዋል።

የመንግስትን፣ የግሉ ዘርፍንና የዜጎችን የካፒታል አቅምና ዕውቀትን ደምሮ የሚይዙት የህብረት ስራ ማህበራት መሆናቸውን በግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲው በግልጽ መቀመጡን ጠቁመዋል።

ማህበራቱ ግብርናውን በማሻገር የአርሶና አርብቶ አደሩን ህይወት መቀየር ረገድ ትልቅ አቅም እንዳላቸው ገልፀው የፋይናንስ አቅርቦት ችግርን በመፍታትና የግብይት ሰንሰለቱን በማሳጠር የሸማቹን ህብረተሰብ ሸክም እንደሚያቀሉም አስረድተዋል።

በንቅናቄ መድረኩ የተሳተፉት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ህብረት ስራ ኤጀንሲ የህብረት ስራ ማህበራት ማደራጃና ማስፋፊያ ዳይሬክተር አቶ ቶንጃ ቶማ በበኩላቸው፤ ማህበራቱ ገበያን በማረጋጋት፣ የአርሶ አደሩን ምርታማነት የሚያሳድጉ ግብዓት በማቅረብና በሌሎች ዘርፎች አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው ብለዋል።


በተለይ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የማህበራቱን አቅም ለማሳደግ በተደረገ የሪፎርም ስራ በኢኮኖሚው ውስጥ ያላቸው አበርክቶ እንዲያድግ ማድረጉን ተናግረዋል።

የኦሮሚያ ክልል ህብረት ስራ ልማት ኤጀንሲ ተወካይ ወይዘሮ ሹሬ እጅቢቾ፤ በክልሉ የህብረት ስራ ማህበራትን አሰራር፣ አደረጃጀትና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ በማተኮር ሪፎርም መሰራቱን ገልጸዋል፡፡


በዚህም ጠንካራ ማህበራት እንዲኖሩ አንድ ላይ የማደራጀት ስራ መሰራቱን ጠቅሰው በንቅናቄ መድረኩ የተገኘውን ልምድና እውቀት ተግባራዊ በማድረግ ለማህበራት ውጤታማነት እንደሚሰሩም ተናግረዋል፡፡

የሲዳማ ክልል ህብረት ስራ ኤጀንሲ የህብረት ስራ ማህበራት ማደራጃና ማስፋፊያ ዳይሬክተር አቶ ደምበሎ ዶንጊሶ በበኩላቸው፤ በሪፎርሙ የማህበራቱን ትርፋማነት፣ የአባላት ተጠቃሚነት ከማጎልበት አንጻር ለውጥ ማምጣት ተችሏል ብለዋል።


ከዚህም ባለፈ በአሰራር ስርዓት በአመራርና በአደረጃጀት የጠነከሩና የፋይናንስ አያያዛቸውን ያዘመኑ ማህበራት መፍጠር እንደተቻለ ገልጸው የተገኘውን ውጤት አጠናክሮ ለማስቀጠል የንቅናቄ መድረኩ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ነው የገለጹት።

ላለፉት ስምንት ቀናት በሀዋሳ ሲካሄድ በቆየው መድረክ ላይ ከሲዳማ፣ ከደቡብ ኢትዮጵያና ከኦሮሚያ ክልል የተውጣጡ 900 የቀበሌ ህብረት ስራ ማህበራት አደረጃጀት ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026