የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የመንግስት ሰራተኞች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና መውሰዳቸው በቴክኖሎጂ መስክ የመወዳደር አቅማቸውን ለማሳደግ አስችሏል

Apr 30, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ገንዳውኃ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና መውሰዳቸው በቴክኖሎጂ መስክ አቅማቸውን በማሳደግ ተወዳዳሪነታቸው እንዲጨምር ማድረጉን በምዕራብ ጎንደር ዞን የሚገኙ የመንግስት ሰራተኞች ገለጹ።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ኢንሼቲቭ በመላው ሀገሪቷ የተጀመረው የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና በቴክኖሎጂ የበቃና ተወዳዳሪ የሰው ሀይልን ለማፍራት አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።

5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን ተጠቃሚ ለማድረግ ያለመው ሀገር አቀፍ ስልጠና ዲጂታል ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግም አበርክቶው የላቀ ነው።

ስልጠናው ፕሮግራሚንግ፣ በዳታ ሳይንስ፣ በአንድሮይድና በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መስኮች ዜጎች ባሉበት ቦታ በበይነ-መረብ የሚከታተሉት ነው።

በምዕራብ ጎንደር ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ባለሙያ የሆኑት አቶ ብሩክ ወርቄ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው በመሆኑ ተወዳዳሪ ለመሆን የሚያስችል ነው።

ስልጠናው የቴክኖሎጂ እውቀትንና ክህሎትን በማሳደግ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ ቀልጣፋና ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን በተግባር አረጋግጠናል ነው ያሉት።

​​በዞኑ የመተማ ወረዳ አስተዳደር ሰራተኛ የሆኑት ወይዘሮ ሳራ ወንድሙ በበኩላቸው፤ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ዓለም ካለበት የስልጣኔ ደረጃ እኩል ለመራመድ የሚያስችል ነው ብለዋል።

"አለም በቴክኖሎጂ እየተመራች ባለችበት በዚህ ወቅት፣ እኛም እንደ አንድ የመንግስት ሰራተኛ ራሳችንን ማዘመንና ማብቃት ይጠበቅብናል" ነው ያሉት።

ባገኙት ስልጠና ተጠቅመውም መረጃዎችን በዲጂታል ዘዴ በመሰብሰብ፣ በማቀናበርና ለተገልጋዩ ህብረተሰብ ቀልጣፋ ምላሽ ከመስጠት አንፃር አዲስ እይታ የፈጠረላቸው መሆኑን ተናግረዋል።

​በዞኑ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቡድን መሪ አቶ ስሜነው ተላከ ፤ ስልጠናው የኮምፒውተር ፕሮግራሚንግና የዳታ አያያዝ ተግባራቸውን ለማቅለል እንዳስቻላቸው አስረድተዋል።

ስልጠናው የላቀ ቅልጥፍና እና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት ከማስቻሉም በላይ አለምአቀፍ እውቅና ያለው የምስክር ወረቀት በማግኘታቸው ተወዳዳሪነታቸው ለማሳደግ አስችሎናል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026