🔇Unmute
ጋምቤላ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የበጀት አስተዳደርና አጠቃቀምን በማዘመን በህዝብ ለሚነሱ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ የመስጠቱ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለጸ።
በፕሮግራም በጀት አሰራርና አተገባበር ዙሪያ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች የተሳተፉበት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ዛሬ በጋምቤላ ከተማ እየተካሄደ ነው።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ተወካይ አቶ ኡቶው ኡኮት በመድረኩ ላይ እንዳሉት ፤በክልሉ እየተመዘገበ ያለውን ኢኮኖሚያዊ እድገት ለማስቀጠል የበጀት አስተዳደርና አጠቃቀምን ማዘመን ያስፈልጋል ።
ለዚህም ክልሉ ያለውን ውስን በጀት በአግባቡ በማስተዳደር በህዝብ ለሚነሱ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ተግቶ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።
በዚህ ረገድ ክልሉ ባለፉት ዓመታት ያለውን ውስን በጀት ስራ ላይ በማዋል የህዝቡን የማህበራዊና የኢኮኖሚያዊ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።
በቀጣይም የፋይናንስ አሰራርና አጠቃቀም ሂደቱን ይበልጥ በማዘመን የክልሉን ልማትና እድገት ለማፋጠን በቁርጠኝነት ሊሰራ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።
መንግስት እቅድና በጀት ከውጤት ጋር በማስተሳሰር ቀጣይነት ያለውና ተጨባጭ ውጤት ለማስመዝግብ የሚያስችል’’የፕሮግራም በጀት’’ፖሊሲ ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩንም ገልጸዋል።
በመሆኑም እንደ ሀገር ለተጀመረው የፕሮግራም በጀት ማሻሻያ ፖሊሲ ትግበራ ስኬታማነት የክልሉ አመራሮችና ባለሙያዎች በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ ተወካዩ አስገንዝበዋል።
የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ኡማን አሙሉ (ዶ/ር) በበኩላቸው ፤ባለፉት ዓመታት ሲተገበር የቆየው የበጀት አጠቃቀምና አሰራር በርካታ ለውጦች የታዩበት ነው ብለዋል።
ቀልጠፋና ውጤታማ የበጀት አስተዳደርን ከማስፈን አንፃር ውስንነቶች እንደነበሩ አመልክተው ይሕንን ለመቀየር ይሰራል ነው ያሉት።
በአሁኑ ወቅት በክልሉ የሚተገበረው የፕሮግራም በጀት ቀደም ሲል የነበሩ ክፍተቶችን እንደሚያስቀር ጠቁመው ለተግባራዊነቱ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጠይቀዋል።
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...
Apr 14, 2026
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026