የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በክልሉ የበጀት አስተዳደርና አጠቃቀምን በማዘመን በህዝብ ለሚነሱ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ የመስጠቱ ተግባር ይጠናከራል

Apr 30, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጋምቤላ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የበጀት አስተዳደርና አጠቃቀምን በማዘመን በህዝብ ለሚነሱ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ የመስጠቱ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለጸ።

በፕሮግራም በጀት አሰራርና አተገባበር ዙሪያ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች የተሳተፉበት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ዛሬ በጋምቤላ ከተማ እየተካሄደ ነው።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ተወካይ አቶ ኡቶው ኡኮት በመድረኩ ላይ እንዳሉት ፤በክልሉ እየተመዘገበ ያለውን ኢኮኖሚያዊ እድገት ለማስቀጠል የበጀት አስተዳደርና አጠቃቀምን ማዘመን ያስፈልጋል ።

ለዚህም ክልሉ ያለውን ውስን በጀት በአግባቡ በማስተዳደር በህዝብ ለሚነሱ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ተግቶ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።

በዚህ ረገድ ክልሉ ባለፉት ዓመታት ያለውን ውስን በጀት ስራ ላይ በማዋል የህዝቡን የማህበራዊና የኢኮኖሚያዊ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።

በቀጣይም የፋይናንስ አሰራርና አጠቃቀም ሂደቱን ይበልጥ በማዘመን የክልሉን ልማትና እድገት ለማፋጠን በቁርጠኝነት ሊሰራ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

መንግስት እቅድና በጀት ከውጤት ጋር በማስተሳሰር ቀጣይነት ያለውና ተጨባጭ ውጤት ለማስመዝግብ የሚያስችል’’የፕሮግራም በጀት’’ፖሊሲ ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩንም ገልጸዋል።

በመሆኑም እንደ ሀገር ለተጀመረው የፕሮግራም በጀት ማሻሻያ ፖሊሲ ትግበራ ስኬታማነት የክልሉ አመራሮችና ባለሙያዎች በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ ተወካዩ አስገንዝበዋል።

የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ኡማን አሙሉ (ዶ/ር) በበኩላቸው ፤ባለፉት ዓመታት ሲተገበር የቆየው የበጀት አጠቃቀምና አሰራር በርካታ ለውጦች የታዩበት ነው ብለዋል።

ቀልጠፋና ውጤታማ የበጀት አስተዳደርን ከማስፈን አንፃር ውስንነቶች እንደነበሩ አመልክተው ይሕንን ለመቀየር ይሰራል ነው ያሉት።

በአሁኑ ወቅት በክልሉ የሚተገበረው የፕሮግራም በጀት ቀደም ሲል የነበሩ ክፍተቶችን እንደሚያስቀር ጠቁመው ለተግባራዊነቱ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የማዕድን ሀብት ልማት ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ አቅም እየሆነ ነው

ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...

Jun 10, 2026

የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ የሕዝብን ሀብት ለልማት በማዋል በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...

Jun 9, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...

May 28, 2026

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026