🔇Unmute
ጋምቤላ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የበጀት አስተዳደርና አጠቃቀምን በማዘመን በህዝብ ለሚነሱ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ የመስጠቱ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለጸ።
በፕሮግራም በጀት አሰራርና አተገባበር ዙሪያ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች የተሳተፉበት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ዛሬ በጋምቤላ ከተማ እየተካሄደ ነው።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ተወካይ አቶ ኡቶው ኡኮት በመድረኩ ላይ እንዳሉት ፤በክልሉ እየተመዘገበ ያለውን ኢኮኖሚያዊ እድገት ለማስቀጠል የበጀት አስተዳደርና አጠቃቀምን ማዘመን ያስፈልጋል ።
ለዚህም ክልሉ ያለውን ውስን በጀት በአግባቡ በማስተዳደር በህዝብ ለሚነሱ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ተግቶ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።
በዚህ ረገድ ክልሉ ባለፉት ዓመታት ያለውን ውስን በጀት ስራ ላይ በማዋል የህዝቡን የማህበራዊና የኢኮኖሚያዊ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።
በቀጣይም የፋይናንስ አሰራርና አጠቃቀም ሂደቱን ይበልጥ በማዘመን የክልሉን ልማትና እድገት ለማፋጠን በቁርጠኝነት ሊሰራ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።
መንግስት እቅድና በጀት ከውጤት ጋር በማስተሳሰር ቀጣይነት ያለውና ተጨባጭ ውጤት ለማስመዝግብ የሚያስችል’’የፕሮግራም በጀት’’ፖሊሲ ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩንም ገልጸዋል።
በመሆኑም እንደ ሀገር ለተጀመረው የፕሮግራም በጀት ማሻሻያ ፖሊሲ ትግበራ ስኬታማነት የክልሉ አመራሮችና ባለሙያዎች በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ ተወካዩ አስገንዝበዋል።
የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ኡማን አሙሉ (ዶ/ር) በበኩላቸው ፤ባለፉት ዓመታት ሲተገበር የቆየው የበጀት አጠቃቀምና አሰራር በርካታ ለውጦች የታዩበት ነው ብለዋል።
ቀልጠፋና ውጤታማ የበጀት አስተዳደርን ከማስፈን አንፃር ውስንነቶች እንደነበሩ አመልክተው ይሕንን ለመቀየር ይሰራል ነው ያሉት።
በአሁኑ ወቅት በክልሉ የሚተገበረው የፕሮግራም በጀት ቀደም ሲል የነበሩ ክፍተቶችን እንደሚያስቀር ጠቁመው ለተግባራዊነቱ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጠይቀዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026