የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዘው የተቀናጀ የሚዲያ ሬጉላቶሪና አስተዳደር ስርዓት ሐሰተኛ መረጃን ለመከላከል ጉልህ ሚና አለው

May 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 23/2018 (ኢዜአ)፦ በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዘው የተቀናጀ የሚዲያ ሬጉላቶሪ እና የአስተዳደር ስርዓት ሐሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግርን ለመከላከልና መቆጣጠር ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሃይማኖት ዘለቀ ገለጹ።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ከኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ጋር በመተባበር ያለማውን የተቀናጀ የሚዲያ ሬጉላቶሪ እና አስተዳደር ስርዓት ቴክኖሎጂ የማስጀመሪያ መርሐ ግብር በመካሄድ ላይ ነው።


በመርሐ ግብሩ ላይ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ፣ የብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል እና የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ቦርድ ሰብሳቢ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን፣ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ፣ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሃይማኖት ዘለቀ፣ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር)፣ የመገናኛ ብዙኃን የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል።

ተቀናጀ የሚዲያ ሬጉላቶሪ እና አስተዳደር ስርዓት ቴክኖሎጂ ወደ ተግባር እንዲገባ መደረጉ የባለስልጣኑን እና የዘርፉን ሥራዎች ዘመናዊ ወደ ሆነ አዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግር መሆኑ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሃይማኖት ዘለቀ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ቴክኖሎጂው የተቋሙን ተልዕኮ ለማሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው።

የተቀናጀ የሚዲያ ሬጉላቶሪ እና የአስተዳደር ስርዓት የመገናኛ ብዙኃን የክትትልና የቁጥጥር ሥርዓትን እንደሚያዘምን ገልጸው፥ ኢትዮጵያ እየተገበረች ካለው የዲጂታላይዜሽን ሥርዓት ጋር የተጣጣመ ነው ብለዋል።

የሐሰተኛ መረጃ ስርጭትንና የጥላቻ ንግግርን መከላከልን በሰው ሰራሽ አስተውሎት በመታገዝ ውጤታማ እንደሚያደርግም ጠቁመዋል።

የሚዲያዎችን ሕጋዊነት ለማረጋገጥ እና በዘርፉ ላይ ግልፅ የሆነ የክትትልና ቁጥጥር ስርዓት በመዘርጋት ረገድ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወትም ተናግረዋል።


የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር)፥ ኢንስቲትዩቱ ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ ሰው ሠራሽ አስተውሎት ለሁሉም በሚል መሪ ሀሳብ እየሠራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

የመገናኛ ብዙኃን አሠራርን በማዘመን ሀገራዊ ሚናውን በመወጣት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ዛሬ ይፋ የሆነው የሚዲያ ሬጉላቶሪና አስተዳደር ቴክኖሎጂ ለዘርፉ ዕድገት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የማዕድን ሀብት ልማት ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ አቅም እየሆነ ነው

ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...

Jun 10, 2026

የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ የሕዝብን ሀብት ለልማት በማዋል በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...

Jun 9, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...

May 28, 2026

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026