የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዘው የተቀናጀ የሚዲያ ሬጉላቶሪና አስተዳደር ስርዓት ሐሰተኛ መረጃን ለመከላከል ጉልህ ሚና አለው

May 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 23/2018 (ኢዜአ)፦ በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዘው የተቀናጀ የሚዲያ ሬጉላቶሪ እና የአስተዳደር ስርዓት ሐሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግርን ለመከላከልና መቆጣጠር ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሃይማኖት ዘለቀ ገለጹ።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ከኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ጋር በመተባበር ያለማውን የተቀናጀ የሚዲያ ሬጉላቶሪ እና አስተዳደር ስርዓት ቴክኖሎጂ የማስጀመሪያ መርሐ ግብር በመካሄድ ላይ ነው።


በመርሐ ግብሩ ላይ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ፣ የብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል እና የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ቦርድ ሰብሳቢ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን፣ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ፣ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሃይማኖት ዘለቀ፣ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር)፣ የመገናኛ ብዙኃን የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል።

ተቀናጀ የሚዲያ ሬጉላቶሪ እና አስተዳደር ስርዓት ቴክኖሎጂ ወደ ተግባር እንዲገባ መደረጉ የባለስልጣኑን እና የዘርፉን ሥራዎች ዘመናዊ ወደ ሆነ አዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግር መሆኑ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሃይማኖት ዘለቀ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ቴክኖሎጂው የተቋሙን ተልዕኮ ለማሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው።

የተቀናጀ የሚዲያ ሬጉላቶሪ እና የአስተዳደር ስርዓት የመገናኛ ብዙኃን የክትትልና የቁጥጥር ሥርዓትን እንደሚያዘምን ገልጸው፥ ኢትዮጵያ እየተገበረች ካለው የዲጂታላይዜሽን ሥርዓት ጋር የተጣጣመ ነው ብለዋል።

የሐሰተኛ መረጃ ስርጭትንና የጥላቻ ንግግርን መከላከልን በሰው ሰራሽ አስተውሎት በመታገዝ ውጤታማ እንደሚያደርግም ጠቁመዋል።

የሚዲያዎችን ሕጋዊነት ለማረጋገጥ እና በዘርፉ ላይ ግልፅ የሆነ የክትትልና ቁጥጥር ስርዓት በመዘርጋት ረገድ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወትም ተናግረዋል።


የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር)፥ ኢንስቲትዩቱ ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ ሰው ሠራሽ አስተውሎት ለሁሉም በሚል መሪ ሀሳብ እየሠራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

የመገናኛ ብዙኃን አሠራርን በማዘመን ሀገራዊ ሚናውን በመወጣት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ዛሬ ይፋ የሆነው የሚዲያ ሬጉላቶሪና አስተዳደር ቴክኖሎጂ ለዘርፉ ዕድገት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026