የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ዩኒቨርሲቲው ሀገር በቀል እውቀቶች ለሀገር ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት ግብዓት እንሆዲኑ እየሰራ ነው

May 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አምቦ፤ ሚያዝያ 23/ 2018 (ኢዜአ)፦ አምቦ ዩኒቨርሲቲ ሀገር በቀል እውቀቶችን ከሳይንስ ጋር በማቀናጀት ለሀገር ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት ግብዓት እንዲሆኑ በጥናት እያገዘ መሆኑን አስታወቀ ።

አምቦ ዩኒቨርሲቲ ሀገር በቀል እውቀቶች ለዘላቂ ልማት በሚል መሪ ቃል 11ኛውን ሀገር አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ እይካሄደ ነው።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ባይሳ ለታ (ዶ/ር) በኮንፈረንሱ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር እንገለጹት ዩኒቨርሲቲው የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ብቁ እና ተወዳዳሪ ዜጋ ለማፍራት በትኩረት እየሰራ ነው።

በተለይም በምርምር ስራዎቹ በማህበረሰቡ ውስጥ የሚታዩ ተጨባጭ ችግሮች እንዲፈቱ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

ዩኒቨርሲቲው በጤና፣ በግብርና፣ በባህልና በአስተዳደር ዘርፎች ያሉ ሀገር በቀል እውቀቶችን ከዘመናዊ ሳይንስ ጋር በማቀናጀት ለሀገር ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት ግብዓት እንዲሆኑ የጥናት ውጤቶችን እያበረከተ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

የዛሬው የምርምር ከንፍረንስም የማህበረሰቡን ሀገር በቀል እውቀትን በማጥናት ከዘመናዊ ሳይንስ ጋር በማስተሳሰር ችግር ፈቺ የሚሆንበትን አቅም ለማጎልበት ያለመ ነው ብለዋል።

በአምቦ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት ሰለሞን ማሾ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ በዘንድሮው ኮንፈረንስ ከተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትና የምርምር ማዕከላት የተውጣጡ ምሁራንና ተመራማሪዎች ያጠኗቸው በርካታ የጥናት ፅሁፎች ለውይይት እንደሚቀርቡ ገልጸዋል።

የቀረቡት ጥናቶች በዋናነት ሀገር በቀል እውቀቶች ላይ ትኩረት ያደረጉና በተግባር ሲተረጎሙም የህብረተሰቡን የእለት ተእለት ችግር የመፍታት አቅማቸው ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።

ኮንፈረንሱም እውቀቶቹ ከዘመናዊ ሳይንስ ጋር ተቀናጅተው ጥቅም ላይ የሚውሉበትን ሂደት ለማቀላጠፍና በተመራማሪዎች መካከል የልምድ ልውውጥ እንዲኖር ለማድረግ አቅም እንደሚፈጥር ጠቁመዋል።

በመድረኩ ላይ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የመጡ ተመራማሪዎች፣ የዘርፉ ባለሙያዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የታደሙ ሲሆን፣ ለሁለት ቀናት በሚቆየው ኮንፈረንስ በተመረጡ ዘርፎች ላይ ያተኮሩ የጥናት ውጤቶች ቀርበው ውይይት እንደሚደረግባቸው ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የማዕድን ሀብት ልማት ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ አቅም እየሆነ ነው

ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...

Jun 10, 2026

የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ የሕዝብን ሀብት ለልማት በማዋል በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...

Jun 9, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...

May 28, 2026

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026